سورة المدثر

الترجمة الأمهرية

የሱራ المدّثر ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
Verse 2
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
Verse 6
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
Verse 7
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
Verse 8
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
Verse 9
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
Verse 10
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
Verse 11
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
Verse 12
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
Verse 13
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
Verse 14
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
Verse 17
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
Verse 18
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
Verse 20
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
Verse 21
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
Verse 22
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
Verse 23
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 26
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
Verse 27
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
Verse 28
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
Verse 29
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
Verse 30
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
Verse 32
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
Verse 35
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
Verse 36
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
Verse 39
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 40
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
Verse 41
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
Verse 42
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
Verse 44
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
Verse 45
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
Verse 46
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
Verse 47
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
Verse 48
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
Verse 50
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
Verse 54
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
Verse 55
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
تقدم القراءة