سورة المدثر

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ المدّثر ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
Verse 2

ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
Verse 6

ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
Verse 7

ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
Verse 8

በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
Verse 9

ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
Verse 10

በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
Verse 11

አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
Verse 12

ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
Verse 13

(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
Verse 14

ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡

ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
Verse 17

በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
Verse 18

እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
Verse 20

ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
Verse 21

ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
Verse 22

ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
Verse 23

ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡

አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 26

በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
Verse 27

ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
Verse 28

(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
Verse 29

ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
Verse 30

በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
Verse 32

(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
Verse 35

እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
Verse 36

ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡

ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
Verse 39

የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 40

(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
Verse 41

ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
Verse 42

(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»

(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
Verse 44

«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
Verse 45

«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
Verse 46

«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
Verse 47

«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
Verse 48

የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡

ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
Verse 50

እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡

ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
Verse 54

ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
Verse 55

ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
تقدم القراءة