የሱራ المدّثر ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﮪﮫ
ﮬ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
Verse 2
ﮭﮮ
ﮯ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
Verse 3
ﮰﮱ
ﯓ
ጌታህንም አክብር፡፡
Verse 4
ﯔﯕ
ﯖ
ልብስህንም አጥራ፡፡
Verse 5
ﯗﯘ
ﯙ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
Verse 6
ﯚﯛﯜ
ﯝ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
Verse 7
ﯞﯟ
ﯠ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
Verse 8
ﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
Verse 9
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
Verse 10
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
Verse 11
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
Verse 12
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
Verse 13
ﯺﯻ
ﯼ
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
Verse 14
ﯽﯾﯿ
ﰀ
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
Verse 15
ﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
Verse 16
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋ
ﰌ
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
Verse 17
ﰍﰎ
ﰏ
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
Verse 18
ﰐﰑﰒ
ﰓ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
Verse 19
ﭑﭒﭓ
ﭔ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
Verse 20
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
Verse 21
ﭚﭛ
ﭜ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
Verse 22
ﭝﭞﭟ
ﭠ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
Verse 23
ﭡﭢﭣ
ﭤ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
Verse 24
ﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 25
ﭬﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
Verse 26
ﭲﭳ
ﭴ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
Verse 27
ﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
Verse 28
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
Verse 29
ﭿﮀ
ﮁ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
Verse 30
ﮂﮃﮄ
ﮅ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
Verse 32
ﯥﯦ
ﯧ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
Verse 33
ﯨﯩﯪ
ﯫ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
Verse 34
ﯬﯭﯮ
ﯯ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
Verse 35
ﯰﯱﯲ
ﯳ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
Verse 36
ﯴﯵ
ﯶ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
Verse 37
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
Verse 38
ﯿﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
Verse 39
ﰅﰆﰇ
ﰈ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 40
ﰉﰊﰋ
ﰌ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
Verse 41
ﰍﰎ
ﰏ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
Verse 42
ﰐﰑﰒﰓ
ﰔ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
Verse 43
ﰕﰖﰗﰘﰙ
ﰚ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
Verse 44
ﰛﰜﰝﰞ
ﰟ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
Verse 45
ﰠﰡﰢﰣ
ﰤ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
Verse 46
ﰥﰦﰧﰨ
ﰩ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
Verse 47
ﰪﰫﰬ
ﰭ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
Verse 48
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
Verse 49
ﭖﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
Verse 50
ﭜﭝﭞ
ﭟ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
Verse 51
ﭠﭡﭢ
ﭣ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
Verse 52
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
Verse 53
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
Verse 54
ﭵﭶﭷ
ﭸ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
Verse 55
ﭹﭺﭻ
ﭼ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
Verse 56
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
تقدم القراءة