የሱራ نوح ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
እኛ ኑሕን «ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ በማለት ወደ ሕዝቦቹ ላክነው፡፡»
Verse 2
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
(እርሱም) አለ «ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ለእናንተ ገላጭ የኾንኩ አስጠንቃቂ ነኝ፡፡
Verse 3
ﮎﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
«አላህን ተገዙት፣ ፍሩትም፣ ታዘዙኝም በማለት፤ (አስጠንቃቂ ነኝ)፡፡
Verse 4
«ለእናንተ ከኀጢኣቶቻችሁ ይምራልና፡፡ ወደተወሰነው ጊዜም ያቆያችኋል፡፡ የአላህ (የወሰነው) ጊዜ በመጣ ወቅት አይቆይም፡፡ የምታውቁት ብትኾኑ ኖሮ (በታዘዛችሁ ነበር)፡፡»
Verse 5
(ስለ ተቃወሙትም) «አለ ጌታዬ ሆይ! እኔ ሌሊትም ቀንም ሕዝቦቼን ጠራሁ፡፡
Verse 6
ﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
«ጥሪየም መሸሽን እንጅ ሌላ አልጨመረላቸውም፡፡
Verse 7
«እኔም ለእነርሱ ትምር ዘንድ (ወደ እምነት) በጠራኋቸው ቁጥር ጣቶቻቸውን በጆሮዎቻቸው ውስጥ አደረጉ፡፡ ልብሶቻቸውንም ተከናነቡ፡፡ (በመጥፎ ሥራቸው ላይ) ዘወተሩም፡፡ (ያለ ልክ) መኩራትንም ኮሩ፡፡
Verse 8
ﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
«ከዚያም እኔ በጩኸት ጠራኋቸው፡፡
Verse 9
«ከዚያም እኔ ለእነርሱ ገለጽኩ፡፡ ለእነርሱም መመስጠርን መሰጠርኩ
Verse 10
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡
Verse 11
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
«በእናንተ ላይ ዝናምን ተከታታይ አድርጎ ይልካል፡፡
Verse 12
«በገንዘቦችና በልጆችም ይለግሰላችኋል፡፡ ለእናንተም አትክልቶችን ያደርግላችኋል፡፡ ለእናንተም ወንዞችን ያደርግላችኋል፡፡»
Verse 13
ﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
ﭦ
ለአላህ ልቅናን የማትሹት ለእናንተ ምን አላችሁ?
Verse 14
ﭧﭨﭩ
ﭪ
በልዩ ልዩ ኹኔታዎች በእርግጥ የፈጠራችሁ ሲኾን፡፡
Verse 15
አላህ ሰባትን ሰማያት አንዱ ካንዱ በላይ ሲኾን እንዴት እንደፈጠረ አታዩምን?
Verse 16
በውስጣቸውም ጨረቃን አብሪ አደረገ፡፡ ፀሐይንም ብርሃን አደረገ፡፡
Verse 17
ﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
አላህም ከምድር ማብቀልን አበቀላችሁ፡፡
Verse 18
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
ከዚያም በውስጧ ይመልሳችኋል፡፡ ማውጣትንም ያወጣችኋል፡፡
Verse 19
ﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
አላህም ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ አደረጋት፡፡
Verse 20
ﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ከእርሷ ሰፋፊዎችን መንገዶች ትገቡ ዘንድ፡፡
Verse 21
ኑሕ አለ፡- «ጌታዬ ሆይ! እነሱ አምመጹብኝ፡፡ ገንዘቡና ልጁም ከጥፋት በስተቀር ያልጨመረለትን ሰው ተከተሉ፡፡
Verse 22
ﮡﮢﮣ
ﮤ
«ታላቅንም ተንኮል የመከሩትን ሰዎች» (ተከተሉ)፡፡
Verse 23
አሉም «አምላኮቻችሁን አትተዉ፡፡ ወድንም፣ ሱዋዕንም፣ የጉሥንም፣ የዑቅንም ነስርንም አትተው፡፡
Verse 24
«በእርግጥም ብዙዎችን አሳሳቱ፡፡ ከሓዲዎችንም ጥመትን እንጅ ሌላን አትጨምርላቸው» (አለ)፡፡
Verse 25
በኀጢኣቶቻቸው ምክንያት ተሰጠሙ፡፡ እሳትንም እንዲገቡ ተደረጉ፡፡ ለእነርሱም ከአላህ ሌላ የኾኑ ረዳቶችን አላገኙም፡፡
Verse 26
ኑሕም አለ «ጌታዬ ሆይ! ከከሓዲዎቹ በምድር ላይ አንድንም አትተው፡፡
Verse 27
«አንተ ብትተዋቸው ባሮችህን ያሳስታሉና፡፡ ኀጢኣተኛ ከሓዲንም እንጅ ሌላን አይወልዱም፡፡
Verse 28
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ምእመን ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው፤» (አለ)፡፡
تقدم القراءة