የሱራ الإنفطار ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﭑﭒﭓ
ﭔ
ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
Verse 2
ﭕﭖﭗ
ﭘ
ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
Verse 3
ﭙﭚﭛ
ﭜ
ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
Verse 4
ﭝﭞﭟ
ﭠ
መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
Verse 5
ﭡﭢﭣﭤﭥ
ﭦ
ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
Verse 6
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
Verse 7
ﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
Verse 8
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
Verse 9
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
Verse 10
ﭿﮀﮁ
ﮂ
በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
Verse 11
ﮃﮄ
ﮅ
የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
Verse 12
ﮆﮇﮈ
ﮉ
የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
Verse 13
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 14
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 15
ﮔﮕﮖ
ﮗ
በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
Verse 16
ﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
Verse 17
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 18
ﮣﮤﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 19
(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
تقدم القراءة