سورة الشعراء

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الشعراء ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
Verse 2

ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡

አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡

ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡

ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡

በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡

በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡

ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡

(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡

«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡

«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»

(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡

«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡

(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን

«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡

(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡

«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡

«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»

ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»

(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡

(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡

(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡

(ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡

(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡

(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡

(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡

«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡

በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡

እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡

(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡

«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡

አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
Verse 37

«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»

ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡

ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡

«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡

«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡

«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡

ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡

ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
Verse 46

ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
Verse 47

(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡

(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡

(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡

«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»

ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡

ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
Verse 55

«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
Verse 56

«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
Verse 57

አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
Verse 58

ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡

እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
Verse 60

ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡

ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡

(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡

ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
Verse 64

እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡

ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
Verse 66

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 69

በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡

ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡

«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡

(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
Verse 73

«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»

«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
Verse 76

«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»

«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
Verse 78

«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
Verse 79

«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
Verse 80

«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
Verse 81

«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡

ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡

በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡

የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
Verse 87

በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
Verse 90

ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
Verse 91

ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡

ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»

«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
Verse 94

በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
Verse 95

የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
Verse 96

እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-

በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
Verse 98

(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
Verse 99

አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
Verse 100

ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡

ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 104

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 105

የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
Verse 107

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 108

«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 110

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»

(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡

(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡

«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
Verse 114

«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
Verse 115

«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»

«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
Verse 117

(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡

«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»

እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
Verse 120

ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡

በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
Verse 122

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 123

ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
Verse 125

«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 126

«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 128

«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
Verse 129

«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
Verse 130

«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
Verse 131

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 132

«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
Verse 133

«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
Verse 134

«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡

«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»

(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
Verse 137

«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 138

«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡

አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
Verse 140

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 141

ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
Verse 143

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 144

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 146

«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
Verse 147

«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
Verse 148

«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
Verse 149

«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
Verse 150

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
Verse 151

«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡

«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
Verse 153

(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡

«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»

(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡

«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
Verse 157

ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
Verse 159

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 160

የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
Verse 162

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 163

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 165

«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን

«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»

(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
Verse 168

(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
Verse 169

«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
Verse 170

እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
Verse 171

በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡

በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
Verse 175

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 176

የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
Verse 178

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
Verse 179

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
Verse 182

«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡

«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
Verse 184

«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
Verse 185

አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡

«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
Verse 188

«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡

አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
Verse 191

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
Verse 192

እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Verse 193

እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
Verse 194

ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
Verse 195

ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
Verse 196

እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡

የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን

በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
Verse 200

እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
Verse 202

እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
Verse 203

(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
Verse 204

በቅጣታችን ያቻኩላሉን
Verse 205

አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
Verse 206

ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤

ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡

አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
Verse 209

(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
Verse 210

ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
Verse 212

እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
Verse 214

ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡

ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
Verse 217

አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
Verse 218

በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
Verse 219

በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
Verse 220

እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
Verse 223

የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
Verse 224

ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡

እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
Verse 226

እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
تقدم القراءة