سورة النازعات

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ النازعات ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
Verse 2

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
Verse 3

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
Verse 4

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
Verse 5

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Verse 6

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
Verse 7

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Verse 8

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
Verse 9

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
Verse 11

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
Verse 14

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
Verse 19

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
Verse 20

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
Verse 21

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
Verse 22

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
Verse 23

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
Verse 24

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
Verse 28

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
Verse 29

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
Verse 32

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
Verse 33

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
Verse 36

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
Verse 38

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
Verse 39

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
Verse 41

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
Verse 43

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
Verse 44

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
تقدم القراءة