سورة الحاقة

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الحاقة ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
Verse 2

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
Verse 3

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
Verse 4

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
Verse 5

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡

እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡

ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡

ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
Verse 15

በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡

ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡

በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
Verse 21

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
Verse 22

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
Verse 23

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
Verse 26

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
Verse 27

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
Verse 29

«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
Verse 30

«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
Verse 31

«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡

«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»

ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡

ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
Verse 37

ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
Verse 40

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
Verse 46

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
Verse 48

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
Verse 50

እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
Verse 51

እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
تقدم القراءة