سورة الصافات

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الصافات ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Verse 2

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
Verse 3

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
Verse 4

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
Verse 12

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
Verse 14

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 17

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
Verse 18

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
Verse 24

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
Verse 25

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
Verse 26

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
Verse 32

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
Verse 34

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
Verse 38

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
Verse 40

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
Verse 41

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
Verse 42

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
Verse 44

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
Verse 46

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
Verse 48

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
Verse 49

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
Verse 52

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
Verse 54

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
Verse 58

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Verse 63

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
Verse 65

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
Verse 69

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
Verse 70

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
Verse 72

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
Verse 74

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 77

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
Verse 78

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
Verse 80

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 81

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
Verse 82

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Verse 87

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
Verse 88

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
Verse 89

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
Verse 90

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
Verse 92

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
Verse 93

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
Verse 94

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
Verse 95

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
Verse 96

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
Verse 100

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
Verse 101

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
Verse 103

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
Verse 104

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 107

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
Verse 108

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
Verse 109

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
Verse 110

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 111

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 112

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
Verse 114

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
Verse 115

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 116

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
Verse 117

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
Verse 118

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
Verse 119

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
Verse 120

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
Verse 121

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 122

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
Verse 123

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 124

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
Verse 125

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
Verse 126

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
Verse 127

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
Verse 128

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 129

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
Verse 131

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 132

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 133

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 134

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 135

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
Verse 137

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
Verse 138

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
Verse 139

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 140

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 141

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
Verse 142

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
Verse 145

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
Verse 146

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
Verse 148

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
Verse 149

(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
Verse 151

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
Verse 152

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
Verse 153

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
Verse 154

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Verse 156

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
Verse 157

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
Verse 160

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
Verse 161

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
Verse 162

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
Verse 163

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
Verse 165

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 166

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 167

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
Verse 169

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
Verse 170

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 171

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
Verse 172

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 173

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 174

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
Verse 175

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
Verse 176

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Verse 178

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
Verse 179

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
Verse 181

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
Verse 182

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
تقدم القراءة