የሱራ الصافات ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﭑﭒ
ﭓ
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Verse 2
ﭔﭕ
ﭖ
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
Verse 3
ﭗﭘ
ﭙ
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
Verse 4
ﭚﭛﭜ
ﭝ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
Verse 5
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
Verse 6
ﭦﭧﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
Verse 7
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
Verse 8
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
Verse 9
ﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
Verse 10
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
Verse 11
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
Verse 12
ﮙﮚﮛ
ﮜ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
Verse 13
ﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
Verse 14
ﮢﮣﮤﮥ
ﮦ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
Verse 15
ﮧﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 16
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 17
ﯗﯘ
ﯙ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
Verse 18
ﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
Verse 19
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
Verse 20
ﯧﯨﯩﯪﯫ
ﯬ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
Verse 21
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
Verse 22
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
Verse 23
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
Verse 24
ﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
Verse 25
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
Verse 26
ﭖﭗﭘﭙ
ﭚ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
Verse 27
ﭛﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
Verse 28
ﭡﭢﭣﭤﭥﭦ
ﭧ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
Verse 29
ﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
Verse 30
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
Verse 31
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
Verse 32
ﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
Verse 33
ﮇﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
Verse 34
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Verse 35
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
Verse 36
ﮝﮞﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
Verse 37
ﮤﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
Verse 38
ﮪﮫﮬﮭ
ﮮ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
Verse 39
ﮯﮰﮱﯓﯔﯕ
ﯖ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
Verse 40
ﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
Verse 41
ﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
Verse 42
ﯡﯢﯣ
ﯤ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
Verse 43
ﯥﯦﯧ
ﯨ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
Verse 44
ﯩﯪﯫ
ﯬ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
Verse 45
ﯭﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
Verse 46
ﯳﯴﯵ
ﯶ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
Verse 47
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
Verse 48
ﯿﰀﰁﰂ
ﰃ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
Verse 49
ﰄﰅﰆ
ﰇ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
Verse 50
ﰈﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
Verse 51
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
Verse 52
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
Verse 53
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
Verse 54
ﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
Verse 55
ﭣﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
Verse 56
ﭩﭪﭫﭬﭭ
ﭮ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
Verse 57
ﭯﭰﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
Verse 58
ﭶﭷﭸ
ﭹ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
Verse 59
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
Verse 60
ﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
Verse 61
ﮇﮈﮉﮊ
ﮋ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
Verse 62
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Verse 63
ﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
Verse 64
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
Verse 65
ﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
Verse 66
ﮤﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
Verse 67
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
Verse 68
ﯔﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
Verse 69
ﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
Verse 70
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
Verse 71
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
Verse 72
ﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
Verse 73
ﯯﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
Verse 74
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 75
ﯺﯻﯼﯽﯾ
ﯿ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
Verse 76
ﰀﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 77
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
Verse 78
ﭖﭗﭘﭙ
ﭚ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
Verse 79
ﭛﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
Verse 80
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 81
ﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
Verse 82
ﭫﭬﭭ
ﭮ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
Verse 83
ﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
Verse 84
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
Verse 85
ﭻﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
Verse 86
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Verse 87
ﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
Verse 88
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
Verse 89
ﮒﮓﮔ
ﮕ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
Verse 90
ﮖﮗﮘ
ﮙ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
Verse 91
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
Verse 92
ﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
Verse 93
ﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
Verse 94
ﮫﮬﮭ
ﮮ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
Verse 95
ﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
Verse 96
ﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
Verse 97
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
Verse 98
ﯢﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
Verse 99
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
Verse 100
ﯯﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
Verse 101
ﯵﯶﯷ
ﯸ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
Verse 102
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
Verse 103
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
Verse 104
ﭖﭗﭘ
ﭙ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
Verse 105
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 106
ﭣﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
Verse 107
ﭩﭪﭫ
ﭬ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
Verse 108
ﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
Verse 109
ﭲﭳﭴ
ﭵ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
Verse 110
ﭶﭷﭸ
ﭹ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 111
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 112
ﭿﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
Verse 113
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
Verse 114
ﮑﮒﮓﮔﮕ
ﮖ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
Verse 115
ﮗﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 116
ﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
Verse 117
ﮢﮣﮤ
ﮥ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
Verse 118
ﮦﮧﮨ
ﮩ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
Verse 119
ﮪﮫﮬﮭ
ﮮ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
Verse 120
ﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
Verse 121
ﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 122
ﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
Verse 123
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 124
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
Verse 125
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
Verse 126
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
Verse 127
ﭑﭒﭓ
ﭔ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
Verse 128
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 129
ﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
Verse 130
ﭟﭠﭡﭢ
ﭣ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
Verse 131
ﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 132
ﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 133
ﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 134
ﭳﭴﭵﭶ
ﭷ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 135
ﭸﭹﭺﭻ
ﭼ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
Verse 136
ﭽﭾﭿ
ﮀ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
Verse 137
ﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
Verse 138
ﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
Verse 139
ﮋﮌﮍﮎ
ﮏ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 140
ﮐﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 141
ﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
Verse 142
ﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
Verse 143
ﮠﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
Verse 144
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
Verse 145
ﮭﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
Verse 146
ﯔﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
Verse 147
ﯚﯛﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
Verse 148
ﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
Verse 149
ﯦﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
Verse 150
ﯬﯭﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
Verse 151
ﯳﯴﯵﯶﯷ
ﯸ
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
Verse 152
ﯹﯺﯻﯼ
ﯽ
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
Verse 153
ﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
Verse 154
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Verse 155
ﭖﭗ
ﭘ
አትገነዘቡምን?
Verse 156
ﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
Verse 157
ﭞﭟﭠﭡﭢ
ﭣ
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
Verse 158
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
Verse 159
ﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
Verse 160
ﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
Verse 161
ﭺﭻﭼ
ﭽ
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
Verse 162
ﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
Verse 163
ﮃﮄﮅﮆﮇ
ﮈ
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
Verse 164
ﮉﮊﮋﮌﮍﮎ
ﮏ
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
Verse 165
ﮐﮑﮒ
ﮓ
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 166
ﮔﮕﮖ
ﮗ
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 167
ﮘﮙﮚ
ﮛ
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
Verse 168
ﮜﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
Verse 169
ﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
Verse 170
ﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 171
ﮮﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
Verse 172
ﯕﯖﯗ
ﯘ
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 173
ﯙﯚﯛﯜ
ﯝ
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 174
ﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
Verse 175
ﯣﯤﯥ
ﯦ
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
Verse 176
ﯧﯨ
ﯩ
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
Verse 177
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Verse 178
ﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
Verse 179
ﯶﯷﯸ
ﯹ
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
Verse 180
ﯺﯻﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
Verse 181
ﰁﰂﰃ
ﰄ
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
Verse 182
ﰅﰆﰇﰈ
ﰉ
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
تقدم القراءة