سورة الصافات

الترجمة الأمهرية

የሱራ الصافات ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Verse 2
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
Verse 3
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
Verse 4
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
Verse 12
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
Verse 14
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
Verse 17
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
Verse 18
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
Verse 24
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
Verse 25
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
Verse 26
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
Verse 32
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
Verse 34
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
Verse 38
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
Verse 40
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
Verse 41
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
Verse 42
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
Verse 44
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
Verse 46
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
Verse 48
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
Verse 49
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
Verse 52
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
Verse 54
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
Verse 58
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Verse 63
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
Verse 65
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
Verse 69
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
Verse 70
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
Verse 72
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
Verse 74
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 77
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
Verse 78
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
Verse 80
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 81
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
Verse 82
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Verse 87
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
Verse 88
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
Verse 89
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
Verse 90
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
Verse 92
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
Verse 93
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
Verse 94
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
Verse 95
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
Verse 96
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
Verse 100
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
Verse 101
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
Verse 103
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
Verse 104
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 107
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
Verse 108
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
Verse 109
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
Verse 110
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 111
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 112
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
Verse 114
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
Verse 115
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
Verse 116
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
Verse 117
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
Verse 118
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
Verse 119
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
Verse 120
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
Verse 121
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 122
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
Verse 123
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 124
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
Verse 125
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
Verse 126
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
Verse 127
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
Verse 128
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Verse 129
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
Verse 131
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Verse 132
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
Verse 133
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 134
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 135
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
Verse 137
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
Verse 138
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
Verse 139
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Verse 140
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Verse 141
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
Verse 142
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
Verse 145
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
Verse 146
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
Verse 148
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
Verse 149
(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
Verse 151
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
Verse 152
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
Verse 153
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
Verse 154
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Verse 156
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
Verse 157
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
Verse 160
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
Verse 161
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
Verse 162
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
Verse 163
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
Verse 165
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 166
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
Verse 167
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
Verse 169
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
Verse 170
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 171
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
Verse 172
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 173
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Verse 174
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
Verse 175
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
Verse 176
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Verse 178
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
Verse 179
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
Verse 181
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
Verse 182
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
تقدم القراءة