سورة النازعات

الترجمة الأمهرية

የሱራ النازعات ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
Verse 2
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
Verse 3
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
Verse 4
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
Verse 5
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Verse 6
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
Verse 7
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Verse 8
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
Verse 9
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
Verse 11
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
Verse 14
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
Verse 19
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
Verse 20
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
Verse 21
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
Verse 22
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
Verse 23
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
Verse 24
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
Verse 28
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
Verse 29
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
Verse 32
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
Verse 33
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
Verse 36
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
Verse 38
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
Verse 39
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
Verse 41
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
Verse 43
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
Verse 44
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
تقدم القراءة