የሱራ الحاقة ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﮯ
ﮰ
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
Verse 2
ﮱﯓ
ﯔ
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
Verse 3
ﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
Verse 4
ﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
Verse 5
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
Verse 6
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
Verse 7
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
Verse 8
ﯼﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
Verse 9
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
Verse 10
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
Verse 11
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
Verse 12
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
Verse 13
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
Verse 14
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
Verse 15
ﭼﭽﭾ
ﭿ
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
Verse 16
ﮀﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
Verse 17
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
Verse 18
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
Verse 19
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
Verse 20
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
Verse 21
ﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
Verse 22
ﮭﮮﮯ
ﮰ
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
Verse 23
ﮱﯓ
ﯔ
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
Verse 24
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
Verse 25
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
Verse 26
ﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
Verse 27
ﯮﯯﯰ
ﯱ
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
Verse 28
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
Verse 29
ﯸﯹﯺ
ﯻ
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
Verse 30
ﯼﯽ
ﯾ
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
Verse 31
ﯿﰀﰁ
ﰂ
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
Verse 32
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
Verse 33
ﰋﰌﰍﰎﰏﰐ
ﰑ
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
Verse 34
ﰒﰓﰔﰕﰖ
ﰗ
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
Verse 35
ﰘﰙﰚﰛﰜ
ﰝ
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
Verse 36
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
Verse 37
ﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
Verse 38
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
Verse 39
ﭡﭢﭣ
ﭤ
በማታዩትም ነገር፡፡
Verse 40
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
Verse 41
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
Verse 42
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
Verse 43
ﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Verse 44
ﮀﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
Verse 45
ﮆﮇﮈ
ﮉ
በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
Verse 46
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
Verse 47
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
Verse 48
ﮖﮗﮘ
ﮙ
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
Verse 49
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
Verse 50
ﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
Verse 51
ﮥﮦﮧ
ﮨ
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
Verse 52
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
تقدم القراءة