سورة النبأ

الترجمة الأمهرية

የሱራ النبأ ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
Verse 2
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
Verse 3
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
Verse 4
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 5
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
Verse 7
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
Verse 8
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
Verse 9
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
Verse 10
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
Verse 11
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
Verse 12
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
Verse 13
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
Verse 15
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
Verse 16
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
Verse 19
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
Verse 20
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
Verse 22
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
Verse 23
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
Verse 25
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
Verse 26
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
Verse 28
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
Verse 29
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
Verse 31
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
Verse 32
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
Verse 33
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
Verse 34
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
تقدم القراءة