የሱራ التكوير ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭙﭚﭛ
ﭜ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
Verse 2
ﭝﭞﭟ
ﭠ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
Verse 3
ﭡﭢﭣ
ﭤ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
Verse 4
ﭥﭦﭧ
ﭨ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
Verse 5
ﭩﭪﭫ
ﭬ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
Verse 6
ﭭﭮﭯ
ﭰ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
Verse 7
ﭱﭲﭳ
ﭴ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
Verse 8
ﭵﭶﭷ
ﭸ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
Verse 9
ﭹﭺﭻ
ﭼ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
Verse 10
ﭽﭾﭿ
ﮀ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
Verse 11
ﮁﮂﮃ
ﮄ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
Verse 12
ﮅﮆﮇ
ﮈ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
Verse 13
ﮉﮊﮋ
ﮌ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
Verse 14
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
Verse 15
ﮒﮓﮔ
ﮕ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
Verse 16
ﮖﮗ
ﮘ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
Verse 17
ﮙﮚﮛ
ﮜ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
Verse 18
ﮝﮞﮟ
ﮠ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
Verse 19
ﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
Verse 20
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
Verse 21
ﮭﮮﮯ
ﮰ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
Verse 22
ﮱﯓﯔ
ﯕ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
Verse 23
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
Verse 24
ﯛﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
Verse 25
ﯡﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
Verse 26
ﯧﯨ
ﯩ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
Verse 27
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 28
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
Verse 29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
تقدم القراءة