سورة التكوير

الترجمة الأمهرية

የሱራ التكوير ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
Verse 5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
Verse 7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
Verse 8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
Verse 9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
Verse 14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
Verse 15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
Verse 16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
Verse 17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
Verse 18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
Verse 19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
Verse 21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
Verse 22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
Verse 23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
Verse 26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
تقدم القراءة