የሱራ الطور ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﮞ
ﮟ
በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡
Verse 2
ﮠﮡ
ﮢ
በተጻፈው መጽሐፍም፡፡
Verse 3
ﮣﮤﮥ
ﮦ
በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡
Verse 4
ﮧﮨ
ﮩ
በደመቀው ቤትም፡፡
Verse 5
ﮪﮫ
ﮬ
ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡
Verse 6
ﮭﮮ
ﮯ
በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡
Verse 7
ﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
Verse 8
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡
Verse 9
ﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡
Verse 10
ﯠﯡﯢ
ﯣ
ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡
Verse 11
ﯤﯥﯦ
ﯧ
ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡
Verse 12
ﯨﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡
Verse 13
ﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡
Verse 14
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
ﯻ
ይህቺ ያቺ በእርሷ ታስተባብሉባት የነበራችሁት እሳት ናት፡፡
Verse 15
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይህ (ፊት ትሉ እንደነበራችሁት) ድግምት ነውን? ወይስ እናንተ አታዩምን?
Verse 16
ግቧት ታገሱም ወይም አትታገሡ በእናንተ ላይ እኩል ነው፡፡ የምትምመነዱት ትሠሩት የነበራችሁትን (ፍዳ) ብቻ ነው (ይባላሉ)፡፡
Verse 17
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
አላህን ፈሪዎቹ በእርግጥ በገነቶችና በጸጋ ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 18
ጌታቸው በሰጣቸው ጸጋ ተደሳቾች ኾነው (በገነት ውስጥ ናቸው)፡፡ የገሀነምንም ስቃይ ጌታቸው ጠበቃቸው፡፡
Verse 19
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
«ትሠሩት በነበራችሁት ምክንያት ተደሳቾች ኾናችሁ ብሉ፤ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
Verse 20
በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
Verse 21
እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡
Verse 22
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ከሚሹትም ሁሉ እሸትንና ስጋን እንጨምርላቸዋለን፡፡
Verse 23
በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፡፡ በውስጧ ውድቅ ንግግርና መውወንጀልም የለም፡፡
Verse 24
ለነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ (ለማሳለፍ) ይዘዋወራሉ፡፡
Verse 25
ﯓﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
የሚጠያየቁ ኾነውም ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይዞራል፡፡
Verse 26
«እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን» ይላሉ፡፡
Verse 27
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
«አላህም በእኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡
Verse 28
«እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበርን፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና» (ይላሉ)፡፡
Verse 29
(ሰዎችን) አስታውስም፡፡ አንተም በጌታህ ጸጋ ምክንያት ጠንቋይም ዕብድም አይደለህም፡፡
Verse 30
ይልቁንም የሞትን አደጋ በእርሱ የምንጠባበቅበት የኾነ ባለ ቅኔ ነው ይላሉን?
Verse 31
ﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
«ተጠባበቁ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከሚጠባበቁት ነኝ» በላቸው፡፡
Verse 32
አእምሮዎቻቸው በዚህ ያዟቸዋልን? አይደለም በእውነቱ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦች ናቸው፡፡
Verse 33
ወይም «ቀጠፈው ይላሉን?» አይደለም፤ በእውነቱ አያምኑም፡፡
Verse 34
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
እውነተኞችም ቢኾኑ መሰሉ የኾነን ንግግር ያምጡ፡፡
Verse 35
ወይስ ያለ አንዳች (ፈጣሪ) ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን?
Verse 36
ወይስ ሰማያትንና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡
Verse 37
ወይስ የጌታህ ግምጃ ቤቶች እነርሱ ዘንድ ናቸውን? ወይስ እነርሱ አሸናፊዎች ናቸውን?
Verse 38
ወይስ ለእነርሱ በእርሱ ላይ (ከሰማይ) የሚያዳምጡበት መሰላል አላቸውን? አድማጫቸውም (ሰማሁ ቢል) ግልጽን አስረጅ ያምጣ፡፡
Verse 39
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን?
Verse 40
ወይስ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳው የተከበዱ ናቸውን?
Verse 41
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
ወይስ ሩቁ ምስጢር እነርሱ ዘንድ ነውን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
Verse 42
ወይስ ተንኮልን (ባንተ) ይሻሉን? እነዚያም የካዱት እነርሱ በተንኮል ተሸናፊዎች ናቸው፡፡
Verse 43
ወይስ ለእነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ አላቸውን? አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡
Verse 44
ከሰማይም ቁራጭን (በእነርሱ ላይ) ወዳቂ ኾኖ ቢያዩ ኖሮ «ይህ የተደራረበ ደመና ነው» ይሉ ነበር፡፡
Verse 45
ያንንም በእርሱ የሚግገደሉበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡
Verse 46
ተንኮላቸው ከእነርሱ ምንንም የማይጠቅማቸውንና እነርሱም የማይርረዱበትን ቀን (እስከ ሚገናኙ ተዋቸው)፡፡
Verse 47
ለእነዚያ ለበደሉትም ከዚህ ሌላ ቅርብ ቅጣት አልላቸው፡፡ ግን አብዛኛዎቻቸው አያውቁም፡፡
Verse 48
ለጌታህ ፍርድም ታገሥ፡፡ አንተ በጥበቃችን ውስጥ ነህና፡፡ ጌታህንም በምትነሳ ጊዜ ከማመስገን ጋር አወድሰው፡፡
Verse 49
ﰋﰌﰍﰎﰏ
ﰐ
ከሌሊቱም አወድሰው፡፡ በከዋክብት መዳበቂያ ጊዜም (ንጋት ላይ አወድሰው)፡፡
تقدم القراءة