سورة عبس

الترجمة الأمهرية

የሱራ عبس ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
Verse 3
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
Verse 4
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
Verse 6
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
Verse 7
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
Verse 9
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
Verse 10
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
Verse 11
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
Verse 12
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
Verse 13
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
Verse 14
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
Verse 15
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
Verse 16
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
Verse 18
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
Verse 19
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
Verse 20
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
Verse 21
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
Verse 22
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
Verse 25
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
Verse 26
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
Verse 27
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
Verse 28
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
Verse 29
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
Verse 30
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
Verse 31
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
Verse 32
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
Verse 33
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
Verse 38
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
Verse 39
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
Verse 40
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
Verse 41
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
Verse 42
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
تقدم القراءة