سورة المرسلات

الترجمة الأمهرية

የሱራ المرسلات ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 1
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
Verse 2
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
Verse 3
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
Verse 4
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
Verse 5
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
Verse 6
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
Verse 7
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
Verse 8
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
Verse 10
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
Verse 11
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
Verse 12
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
Verse 13
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
Verse 15
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 16
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
Verse 17
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
Verse 18
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Verse 19
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 21
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
Verse 22
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
Verse 23
መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!
Verse 24
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 26
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
Verse 28
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
Verse 32
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
Verse 33
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
Verse 34
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 36
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
Verse 37
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
Verse 40
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 42
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
Verse 44
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Verse 45
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
Verse 47
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 49
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Verse 50
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
تقدم القراءة