سورة الرحمن

الترجمة الأمهرية

የሱራ الرحمن ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية

الترجمة الأمهرية

Verse 2
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Verse 4
መናገርን አስተማረው፡፡
Verse 5
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Verse 6
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Verse 7
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Verse 10
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Verse 12
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Verse 13
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Verse 16
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 17
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Verse 18
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 19
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Verse 20
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Verse 21
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 23
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Verse 25
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 26
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Verse 28
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Verse 30
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 31
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Verse 32
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Verse 34
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Verse 36
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Verse 38
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 40
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Verse 42
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Verse 45
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Verse 47
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 48
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Verse 49
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 50
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 51
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Verse 53
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Verse 55
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 57
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 58
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Verse 59
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 61
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 62
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Verse 63
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Verse 64
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Verse 65
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 66
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 67
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 68
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Verse 69
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 70
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 71
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 72
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Verse 73
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 75
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Verse 77
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
تقدم القراءة