የሱራ الرحمن ትርጉም በالأمهرية ከالترجمة الأمهرية
Verse 1
ﭷ
ﭸ
አል-ረሕማን፤
Verse 2
ﭹﭺ
ﭻ
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Verse 3
ﭼﭽ
ﭾ
ሰውን ፈጠረ፡፡
Verse 4
ﭿﮀ
ﮁ
መናገርን አስተማረው፡፡
Verse 5
ﮂﮃﮄ
ﮅ
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Verse 6
ﮆﮇﮈ
ﮉ
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Verse 7
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
Verse 8
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
Verse 9
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Verse 10
ﮛﮜﮝ
ﮞ
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
Verse 11
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Verse 12
ﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Verse 13
ﮪﮫﮬﮭ
ﮮ
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 14
ﮯﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Verse 15
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
Verse 16
ﯝﯞﯟﯠ
ﯡ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 17
ﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Verse 18
ﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 19
ﭑﭒﭓ
ﭔ
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Verse 20
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Verse 21
ﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 22
ﭟﭠﭡﭢ
ﭣ
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
Verse 23
ﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 24
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Verse 25
ﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 26
ﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
Verse 27
ﭺﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Verse 28
ﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 29
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Verse 30
ﮒﮓﮔﮕ
ﮖ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 31
ﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Verse 32
ﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 33
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Verse 34
ﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 35
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Verse 36
ﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 37
ﯧﯨﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Verse 38
ﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 39
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
Verse 40
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 41
ﰁﰂﰃﰄﰅﰆ
ﰇ
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Verse 42
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
Verse 43
ﭖﭗﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
Verse 44
ﭝﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Verse 45
ﭣﭤﭥﭦ
ﭧ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 46
ﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Verse 47
ﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 48
ﭳﭴ
ﭵ
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Verse 49
ﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 50
ﭻﭼﭽ
ﭾ
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 51
ﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 52
ﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Verse 53
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 54
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Verse 55
ﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 56
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 57
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 58
ﮮﮯﮰ
ﮱ
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Verse 59
ﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 60
ﯘﯙﯚﯛﯜ
ﯝ
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
Verse 61
ﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 62
ﯣﯤﯥ
ﯦ
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Verse 63
ﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Verse 64
ﯬ
ﯭ
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Verse 65
ﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 66
ﯳﯴﯵ
ﯶ
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 67
ﯷﯸﯹﯺ
ﯻ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 68
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Verse 69
ﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 70
ﭑﭒﭓ
ﭔ
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 71
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 72
ﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Verse 73
ﭟﭠﭡﭢ
ﭣ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 74
ﭤﭥﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
Verse 75
ﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
Verse 76
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Verse 77
ﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 78
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
تقدم القراءة