سورة الرحمن

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الرحمن ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 2

ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Verse 4

መናገርን አስተማረው፡፡
Verse 5

ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Verse 6

ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Verse 7

ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡

መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Verse 10

ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡

በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Verse 12

የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Verse 13

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Verse 16

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 17

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Verse 18

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 19

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Verse 20

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Verse 21

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 23

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Verse 25

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 26

በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡

የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Verse 28

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Verse 30

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Verse 31

እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Verse 32

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Verse 34

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Verse 36

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Verse 38

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 40

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Verse 42

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡

ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡

በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Verse 45

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Verse 47

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 48

የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Verse 49

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 50

በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 51

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Verse 53

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Verse 55

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 57

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 58

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Verse 59

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 61

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 62

ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Verse 63

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Verse 64

ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Verse 65

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 66

በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Verse 67

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 68

በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Verse 69

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 70

በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Verse 71

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 72

በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Verse 73

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Verse 75

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?

በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Verse 77

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
تقدم القراءة