سورة الفجر

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الفجر ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


በጎህ እምላለሁ፡፡
Verse 3

በጥንዱም በነጠላውም፡፡
Verse 7

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
Verse 10

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
Verse 11

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
Verse 12

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
Verse 14

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
Verse 19

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
Verse 20

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
Verse 24

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
Verse 26

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
Verse 27

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
Verse 30

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
تقدم القراءة