የሱራ القمر ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation
Verse 1
ﮬﮭﮮﮯ
ﮰ
ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ ጨረቃም ተገመሰ፡፡
Verse 2
ተዓምርንም ቢያዩ (ከእምነት) ይዞራሉ፡፡ (ይህ) «ዘውታሪ ድግምት ነውም» ይላሉ፡፡
Verse 3
አስተባበሉም፡፡ ዝንባሌዎቻቸውንም ተከተሉ፡፡ ነገርም ሁሉ (ወሰን አለው)፤ ረጊ ነው፡፡
Verse 4
ከዜናዎችም በእርሱ ውስጥ መገሰጥ ያለበት ነገር በእርግጥ መጣላቸው፡፡
Verse 5
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ሙሉ የኾነች ጥበብ (መጣቻቸው) ግን አስፈራሪዎቹ አያብቃቁም፡፡
Verse 6
ከነርሱም ዙር፡፡ ጠሪው (መልአክ) ወደ አስደንጋጭ ነገር የሚጠራበትን ቀን (አስታውስ)፡፡
Verse 7
ዓይኖቻቸው ያቀረቀሩ ኾነው፤ ፍጹም የተበተነ አንበጣ መስለው ከመቃብሮቹ ይወጣሉ፡፡
Verse 8
ወደ ጠሪው አንገቶቻቸውን ሳቢዎች ቸኳዮች ኾነው (ይወጣሉ)፡፡ ከሓዲዎቹ (ያን ጊዜ ምን ይላሉ?) «ይህ ብርቱ ቀን ነው» ይላሉ፡፡
Verse 9
ከእነርሱ በፊት የኑሕ ነገድ አስተባበለች፡፡ ባሪያችንንም (ኑሕን) አስተባበሉ፡፡ «ዕብድ ነውም» አሉ፡፡ ተገላመጠም፡፡
Verse 10
ﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ጌታውንም «እኔ የተሸነፍኩ ነኝና እርዳኝ» ሲል ጠራ፡፡
Verse 11
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ወዲያውም የሰማይን ደጃፎች በሚንቧቧ ውሃ ከፈትን፡፡
Verse 12
የምድርንም ምንጮች አፈነዳን፡፡ ውሃውም (የሰማዩና የምድሩ) በእርግጥ በተወሰነ ኹነታ ላይ ተገናኘ፡፡
Verse 13
ﮅﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
ባለ ሳንቃዎችና ባለሚስማሮች በኾነችም ታንኳ ላይ ጫንነው፡፡
Verse 14
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
በጥበቃችን ስር ኾና ትንሻለላለች፡፡ ተክዶ ለነበረው ሰው ምንዳ (ይህንን ሠራን)፡፡
Verse 15
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
ተዓምር አድርገንም በእርግጥ ተውናት፡፡ ከተገሳጭም አልለን?
Verse 16
ﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
Verse 17
ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገንዛቢም አልለን?
Verse 18
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ዓድ አስተባበለች፡፡ ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ!
Verse 19
እኛ በእነርሱ ላይ ዘወትር መናጢ በኾነ ቀን በኀይል የምትንሻሻ ነፋስን ላክንባቸው፡፡
Verse 20
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
ሰዎቹን ልክ ከሥሮቻቸው የተጎለሰሱ የዘንባባ ግንዶች መስለው (ከተደበቁበት) ትነቅላቸዋለች፡፡
Verse 21
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
Verse 22
ቁርኣንንም ለማስታወስ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
Verse 23
ﯬﯭﯮ
ﯯ
ሰሙድ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡
Verse 24
«ከእኛ የኾነን አንድን ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡
Verse 25
«ከኛ መካከል በእርሱ ላይ (ብቻ) ማስገንዘቢያ (ራእይ) ተጣለለትን? አይደለም እርሱ ውሸታም ኩሩ ነው» (አሉ)፡፡
Verse 26
ﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
ውሸታሙ ኩሩው ማን እንደኾነ ነገ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Verse 27
እኛ ሴት ግመልን ለእነርሱ መፈተኛ ትኾን ዘንድ ላኪዎች ነን፡፡ ተጠባበቃቸውም፡፡ ታገስም፡፡
Verse 28
ውሃውንም በመካከላቸው የተከፈለ መኾኑን ንገራቸው፡፡ ከውሃ የኾነ ፋንታ ሁሉ (ተረኞቹ) የሚጣዱት ነው፡፡
Verse 29
ﭛﭜﭝﭞ
ﭟ
ጓደኛቸውንም ጠሩ፡፡ ወዲያውም (ሰይፍን) ተቀበለ፡፡ ወጋትም፡፡
Verse 30
ﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
Verse 31
እኛ በእነርሱ ላይ አንዲትን ጩኸት ላክንባቸው፡፡ ወዲያውም ከበረት አጣሪ (አጥር) እንደ ተሰባበረ ርግጋፊ ኾኑ፡፡
Verse 32
ቁርኣንንም ለመገንዘብ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
Verse 33
ﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
የሉጥ ሕዝብ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡
Verse 34
እኛ በእነርሱ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ላክን፡፡ የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ (እነርሱንስ) በሌሊት መጨረሻ ላይ አዳንናቸው፡፡
Verse 35
ከእኛ በኾነ ጸጋ (አዳንናቸው)፡፡ እንደዚሁ ያመሰገነን ሰው እንመነዳለን፡፡
Verse 36
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
ብርቱይቱን አያያዛችንንም በእርግጥ አስጠነቀቃቸው፡፡ በማስጠንቀቂያዎቹም ተከራከሩ፡፡
Verse 37
ከእንግዶቹም እንዲያስመቻቸው ደጋግመው ፈለጉት፡፡ ወዲያውም ዓይኖቻቸውን አበስን፡፡ «ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (አልናቸው)፡፡
Verse 38
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
በማለዳም ዘውታሪ የኾነ ቅጣት በእርግጥ ማለደባቸው፡፡
Verse 39
ﮥﮦﮧ
ﮨ
«ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (ተባሉ)፡፡
Verse 40
ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
Verse 41
ﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
የፈርዖንንም ቤተሰቦች ማስጠንቀቂያዎች በእርግጥ መጡዋቸው፡፡
Verse 42
በተዓምራቶቻችን በሁሏም አስተባበሉ፡፡ የብርቱ ቻይንም አያያዝ ያዝናቸው፡፡
Verse 43
ከሓዲዎቻችሁ ከእነዚህ በላጮች ናቸውን? ወይስ ለናንተ በመጽሐፎች ውስጥ (የተነገረ) ነፃነት አላችሁን?
Verse 44
ﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ወይስ «እኛ የተረዳን ክምቹዎች ነን» ይላሉን?
Verse 45
ﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ክምቹዎቹ በእርግጥ ድል ይምመታሉ፡፡ ጀርባዎችንም ያዞራሉ፡፡
Verse 46
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
ይልቁንም ሰዓቲቱ (ትንሣኤ) ቀጠሮዋቸው ናት፡፡ ሰዓቲቱም በጣም የከበደችና የመረረች ናት፡፡
Verse 47
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
አመጸኞች በስህተትና በእሳቶች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 48
በእሳት ውስጥ በፊቶቻቸው በሚጎተቱበት ቀን «የሰቀርን መንካት ቅመሱ» (ይባላሉ)፡፡
Verse 49
ﰍﰎﰏﰐﰑ
ﰒ
እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው፡፡
Verse 50
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ትእዛዛችንም እንደ ዓይን ቅጽበት አንዲት (ቃል) እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Verse 51
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ብጤዎቻችሁንም በእርግጥ አጠፋን፡፡ ተገሳጭም አልለን?
Verse 52
ﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
የሠሩትም ነገር ሁሉ በመጽሐፎች ውስጥ ነው፡፡
Verse 53
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
ትንሹም ትልቁም ሁሉ የተጻፈ ነው፡፡
Verse 54
ﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በወንዞች ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 55
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
(እነርሱም ውድቅ ቃልና መውወንጀል በሌለበት) በእውነት መቀመጫ ውስጥ ቻይ የሆነው ንጉሥ ዘንድ ናቸው፡፡
تقدم القراءة