سورة الأعلى

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ الأعلى ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
Verse 2

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
Verse 3

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
Verse 4

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
Verse 5

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
Verse 6

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
Verse 8

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
Verse 9

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
Verse 10

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
Verse 11

መናጢውም ይርቃታል፡፡

ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
Verse 16

ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
Verse 17

መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡

ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
Verse 19

በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
تقدم القراءة