سورة البروج

Sadiq and Sani - Amharic translation

የሱራ البروج ትርጉም በالأمهرية ከSadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

Verse 1


የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
Verse 3

በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
Verse 4

የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
Verse 5

የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
Verse 6

እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡

እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡

ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡

በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡

እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
Verse 12

የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
Verse 13

እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
Verse 14

እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
Verse 15

የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
Verse 18

የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡

በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
Verse 20

አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
Verse 21

ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Verse 22

የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
تقدم القراءة