surah.translation .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡
መቃብሮችን እስከ ጎበኛችሁ ድረስ፡፡
ተከልከሉ፤ ወደፊት (ውጤቱን) ታውቃላችሁ፡፡
ከዚያም ተከልከሉ፤ ወደ ፊት ታውቃላችሁ፡፡
በእውነቱ (የሚጠብቃችሁን) እርግጠኛ ዕውቀትን ብታውቁ ኖሮ፤ (ባልዘናጋችሁ ነበር)፡፡
ገሀነምን በእርግጥ ታያላችሁ፡፡
ከዚያም እርግጠኛን ማየት ታዩዋታላችሁ፡፡
ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡