ترجمة سورة الأعلى

الترجمة الأمهرية
ترجمة معاني سورة الأعلى باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡
መናጢውም ይርቃታል፡፡
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡
Icon