ترجمة معاني سورة النبأ باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
ﰡ
آية رقم 1
ﭑﭒ
ﭓ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
آية رقم 2
ﭔﭕﭖ
ﭗ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
آية رقم 3
ﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
آية رقم 4
ﭝﭞ
ﭟ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
آية رقم 5
ﭠﭡﭢ
ﭣ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
آية رقم 6
ﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
آية رقم 7
ﭩﭪ
ﭫ
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
آية رقم 8
ﭬﭭ
ﭮ
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
آية رقم 9
ﭯﭰﭱ
ﭲ
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
آية رقم 10
ﭳﭴﭵ
ﭶ
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
آية رقم 11
ﭷﭸﭹ
ﭺ
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
آية رقم 12
ﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
آية رقم 13
ﮀﮁﮂ
ﮃ
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
آية رقم 14
ﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
آية رقم 15
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
آية رقم 16
ﮏﮐ
ﮑ
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
آية رقم 17
ﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
آية رقم 18
ﮘﮙﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
آية رقم 19
ﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
آية رقم 20
ﮤﮥﮦﮧ
ﮨ
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
آية رقم 21
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
آية رقم 22
ﮮﮯ
ﮰ
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
آية رقم 23
ﮱﯓﯔ
ﯕ
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
آية رقم 24
ﯖﯗﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
آية رقم 25
ﯝﯞﯟ
ﯠ
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
آية رقم 26
ﯡﯢ
ﯣ
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
آية رقم 27
ﯤﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
آية رقم 28
ﯪﯫﯬ
ﯭ
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
آية رقم 29
ﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
آية رقم 30
ﯳﯴﯵﯶﯷ
ﯸ
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 31
ﭑﭒﭓ
ﭔ
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
آية رقم 32
ﭕﭖ
ﭗ
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
آية رقم 33
ﭘﭙ
ﭚ
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
آية رقم 34
ﭛﭜ
ﭝ
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
آية رقم 35
ﭞﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
آية رقم 36
ﭥﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
آية رقم 37
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
آية رقم 38
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
آية رقم 39
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
آية رقم 40
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
تقدم القراءة