ترجمة معاني سورة النبأ باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية

محمد صادق

الترجمة الأمهرية

محمد صادق

آية رقم 1
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
آية رقم 2
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
آية رقم 3
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
آية رقم 4
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
آية رقم 5
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
آية رقم 6
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
آية رقم 7
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
آية رقم 8
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
آية رقم 9
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
آية رقم 10
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
آية رقم 11
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
آية رقم 12
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
آية رقم 13
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
آية رقم 14
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
آية رقم 15
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
آية رقم 16
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
آية رقم 18
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
آية رقم 19
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
آية رقم 20
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
آية رقم 21
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
آية رقم 22
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
آية رقم 23
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
آية رقم 25
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
آية رقم 26
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
آية رقم 27
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
آية رقم 28
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
آية رقم 29
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
آية رقم 30
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 31
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
آية رقم 32
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
آية رقم 33
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
آية رقم 34
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
آية رقم 35
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
آية رقم 36
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
تقدم القراءة