ترجمة سورة التكوير

الترجمة الأمهرية
ترجمة معاني سورة التكوير باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
Icon