ترجمة معاني سورة التكوير باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية

محمد صادق

الترجمة الأمهرية

محمد صادق

آية رقم 1
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
آية رقم 2
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
آية رقم 3
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
آية رقم 4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
آية رقم 5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
آية رقم 6
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
آية رقم 7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
آية رقم 8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
آية رقم 9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
آية رقم 10
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
آية رقم 11
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
آية رقم 12
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
آية رقم 13
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
آية رقم 14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
آية رقم 15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
آية رقم 16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
آية رقم 17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
آية رقم 18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
آية رقم 19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
آية رقم 20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
آية رقم 21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
آية رقم 22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
آية رقم 23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
آية رقم 24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
آية رقم 25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
آية رقم 26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
آية رقم 27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
تقدم القراءة