ترجمة معاني سورة التكوير باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
ﰡ
آية رقم 1
ﭙﭚﭛ
ﭜ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
آية رقم 2
ﭝﭞﭟ
ﭠ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
آية رقم 3
ﭡﭢﭣ
ﭤ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
آية رقم 4
ﭥﭦﭧ
ﭨ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
آية رقم 5
ﭩﭪﭫ
ﭬ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
آية رقم 6
ﭭﭮﭯ
ﭰ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
آية رقم 7
ﭱﭲﭳ
ﭴ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
آية رقم 8
ﭵﭶﭷ
ﭸ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
آية رقم 9
ﭹﭺﭻ
ﭼ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
آية رقم 10
ﭽﭾﭿ
ﮀ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
آية رقم 11
ﮁﮂﮃ
ﮄ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
آية رقم 12
ﮅﮆﮇ
ﮈ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
آية رقم 13
ﮉﮊﮋ
ﮌ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
آية رقم 14
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
آية رقم 15
ﮒﮓﮔ
ﮕ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
آية رقم 16
ﮖﮗ
ﮘ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
آية رقم 17
ﮙﮚﮛ
ﮜ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
آية رقم 18
ﮝﮞﮟ
ﮠ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
آية رقم 19
ﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
آية رقم 20
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
آية رقم 21
ﮭﮮﮯ
ﮰ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
آية رقم 22
ﮱﯓﯔ
ﯕ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
آية رقم 23
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
آية رقم 24
ﯛﯜﯝﯞﯟ
ﯠ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
آية رقم 25
ﯡﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
آية رقم 26
ﯧﯨ
ﯩ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
آية رقم 27
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 28
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
آية رقم 29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
تقدم القراءة