ترجمة معاني سورة القلم باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
ﰡ
آية رقم 1
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
آية رقم 2
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
آية رقم 3
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
آية رقم 4
ﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
آية رقم 5
ﮠﮡ
ﮢ
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
آية رقم 6
ﮣﮤ
ﮥ
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
آية رقم 7
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
آية رقم 8
ﯓﯔﯕ
ﯖ
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
آية رقم 9
ﯗﯘﯙﯚ
ﯛ
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
آية رقم 10
ﯜﯝﯞﯟﯠ
ﯡ
ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
آية رقم 11
ﯢﯣﯤ
ﯥ
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
آية رقم 12
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
آية رقم 13
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
آية رقم 14
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
آية رقم 15
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
آية رقم 16
ﯾﯿﰀ
ﰁ
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
آية رقم 17
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
آية رقم 18
ﭜﭝ
ﭞ
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
آية رقم 19
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
آية رقم 20
ﭧﭨ
ﭩ
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
آية رقم 21
ﭪﭫ
ﭬ
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
آية رقم 22
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
آية رقم 23
ﭵﭶﭷ
ﭸ
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
آية رقم 24
ﭹﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
آية رقم 25
ﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
آية رقم 26
ﮅﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
آية رقم 27
ﮋﮌﮍ
ﮎ
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
آية رقم 28
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
آية رقم 29
ﮗﮘﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
آية رقم 30
ﮞﮟﮠﮡﮢ
ﮣ
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
آية رقم 31
ﮤﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
آية رقم 32
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
آية رقم 33
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
آية رقم 34
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
آية رقم 35
ﯨﯩﯪ
ﯫ
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
آية رقم 36
ﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
آية رقم 37
ﯱﯲﯳﯴﯵ
ﯶ
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
آية رقم 38
ﯷﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
آية رقم 39
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
آية رقم 40
ﰊﰋﰌﰍ
ﰎ
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
آية رقم 41
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
آية رقم 42
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
آية رقم 43
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
آية رقم 44
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
آية رقم 45
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
آية رقم 46
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
آية رقم 47
ﭹﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
آية رقم 48
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
آية رقم 49
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
آية رقم 50
ﮖﮗﮘﮙﮚ
ﮛ
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
آية رقم 51
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
آية رقم 52
ﮩﮪﮫﮬﮭ
ﮮ
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
تقدم القراءة