ترجمة معاني سورة العاديات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
آية رقم 2

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
آية رقم 3

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
آية رقم 4

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
آية رقم 5

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
آية رقم 6

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
آية رقم 7

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
آية رقم 8

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
آية رقم 10

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
آية رقم 11

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
تقدم القراءة