ترجمة معاني سورة الدّخان باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭑ
ﭒ
ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡
آية رقم 2
ﭓﭔ
ﭕ
አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡
آية رقم 3
እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡
آية رقم 4
ﭠﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
آية رقم 5
ከእኛ ዘንድ የኾነ ትእዛዝ ሲኾን (አወረድነው)፡፡ እኛ (መልክተኞችን) ላኪዎች ነበርን፡፡
آية رقم 6
ከጌታህ በኾነው ችሮታ (ተላኩ)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
آية رقم 7
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ከኾነው (ተላኩ)፡፡ የምታረጋግጡ እንደኾናችሁ (ነገሩ እንዳልነው መኾኑን እወቁ)፡፡
آية رقم 8
ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ያደርጋል፡፡ ይገድላልም፡፡ ጌታችሁ የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው፡፡
آية رقم 9
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
በእውነቱ እነርሱ የሚጫወቱ ሲኾኑ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 10
ﮓﮔﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
ሰማይም በግልጽ ጭስ የምትመጣበትን ቀን ተጠባበቅ፡፡
آية رقم 11
ﮚﮛﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
ሰዎችን የሚሸፍን (በኾነ ጭስ) ይህ አሳማሚ ቅጣት ነው፡፡
آية رقم 12
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
«ጌታችን ሆይ! ከእኛ ላይ ቅጣቱን ግለጥልን፡፡ እኛ አማኞች እንኾናለንና» (ይላሉም)፡፡
آية رقم 13
(ቅጣቱ በወረደ ጊዜ) ለእነርሱ መግገሰጽ እንዴት ይኖራቸዋል? አስረጅ መልክተኛ የመጣቸው ሲኾን (የካዱም ሲኾኑ)፡፡
آية رقم 14
ﮰﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
ከዚያም ከእርሱ የዞሩ፤ (ከሰው) «የተሰተማረ ዕብድ ነው» ያሉም ሲኾኑ፡፡
آية رقم 15
እኛ ቅጣቱን ለጥቂት ጊዜ ገላጮች ነን፡፡ እናንተ (ወደ ክህደታችሁ) በእርግጥ ተመላሾች ናችሁ፡፡
آية رقم 16
ﯠﯡﯢﯣﯤﯥ
ﯦ
ታላቂቱን ብርቱ አያያዝ በምንይዝበት ቀን፤ እኛ ተበቃዮች ነን፡፡
آية رقم 17
ከእነርሱም በፊት የፈርዖንን ሕዝቦች በእርግጥ ሞከርን፡፡ ክቡር መልእክተኛም መጣላቸው፡፡
آية رقم 18
«የአላህን ባሮች ወደኔ አድርሱ፡፡ እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝና፡፡
آية رقم 19
«በአላህም ላይ አትኩሩ፡፡ እኔ ግልጽ የኾነን አስረጅ ያመጣሁላችሁ ነኝና (በማለት መጣላቸው)፡፡
آية رقم 20
ﭜﭝﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
«እኔም እንዳትወግሩኝ በጌታየና በጌታችሁ ተጠብቂያለሁ፡፡
آية رقم 21
ﭣﭤﭥﭦﭧ
ﭨ
«በእኔም ባታምኑ ራቁኝ» (ተዉኝ አለ)፡፡
آية رقم 22
ﭩﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
ቀጥሎም (ስለ ዛቱበት) «እነዚህ አመጸኞች ሕዝቦች ናቸው» (አጥፋቸው) ሲል ጌታውን ለመነ፡፡
آية رقم 23
ﭰﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
(ጌታው) «ባሮቼንም ይዘህ በሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና፡፡
آية رقم 24
«ባሕሩንም የተከፈተ ኾኖ ተወው፡፡ እነርሱ የሚሰጥጠሙ ሰራዊት ናቸውና» (አለው)፡፡
آية رقم 25
ﭾﭿﮀﮁﮂ
ﮃ
ከአትክልቶችና ከምንጮችም ብዙ ነገሮችን ተዉ፡፡
آية رقم 26
ﮄﮅﮆ
ﮇ
ከአዝመራዎችም ከመልካም መቀመጫም፡፡
آية رقم 27
ﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
በእርሷ ተደሳቾች ከነበሩባትም ድሎት (ብዙን ነገር ተዉ)፡፡
آية رقم 28
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
(ነገሩ) እንደዚሁ ኾነ፡፡ ሌሎችንም ሕዝቦች አወረስናት፡፡
آية رقم 29
ሰማይና ምድርም በእነርሱ ላይ አላለቀሱም፡፡ የሚቆዩም አልነበሩም፡፡
آية رقم 30
የእስራኤልንም ልጆች አዋራጅ ከኾነ ስቃይ በእርግጥ አዳንናቸው፡፡
آية رقم 31
ከፈርዖን፤ እርሱ የኮራ ከወሰን አላፊዎቹ ነበርና፡፡
آية رقم 32
ﮭﮮﮯﮰﮱﯓ
ﯔ
ከማወቅም ጋር በዓለማት ላይ በእርግጥ መረጥናቸው፡፡
آية رقم 33
ከታምራቶችም በውስጡ ግልጽ የኾነ ፈተና ያለበትን ሰጠናቸው፡፡
آية رقم 34
ﯝﯞﯟ
ﯠ
እነዚህ (የመካ ከሓዲዎች) በእርግጥ ይላሉ፡-
آية رقم 35
እርሷ የፊተኛይቱ ሞታችን እንጅ አይደለችም፡፡ እኛም የምንቀሰቀስ አይደለንም፡፡
آية رقم 36
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
እውነተኞችም እንደ ኾናችሁ አባቶቻችንን አምጡልን፡፡
آية رقم 37
እነርሱ በላጮች ናቸውን ወይስ የቱብበዕ ሕዝቦችና እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት? አጠፋናቸው፡፡ እነርሱ አመጸኞች ነበሩና፡፡
آية رقم 38
ሰማያትንና ምድርንም በሁለቱ መካከል ያለውንም ሁሉ ቀላጆች ኾነን አልፈጠርንም፡፡
آية رقم 39
ሁለቱንም በምር እንጅ አልፈጠርናቸውም፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡
آية رقم 40
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው፡፡
آية رقم 41
ዘመድ ከዘመዱ ምንንም የማይጠቅምበት እነርሱም የማይርረዱበት ቀን ነው፡፡
آية رقم 42
አላህ ያዘነለት ሰውና ያመነ ብቻ ሲቀር፡፡ (እርሱስ ይርረዳል)፡፡ እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነውና፡፡
آية رقم 43
ﭫﭬﭭ
ﭮ
የዘቁመ ዛፍ
آية رقم 44
ﭯﭰ
ﭱ
የኀጢኣተኛው ምግብ ነው፡፡
آية رقم 45
ﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
እንደ ዘይት አተላ ነው፡፡ በሆዶች ውስጥ የሚፈላ ሲኾን፡፡
آية رقم 46
ﭷﭸ
ﭹ
እንደ ገነፈለ ውሃ አፈላል (የሚፈላ ሲኾን)፡፡
آية رقم 47
ﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ያዙት፤ ወደ ገሀነም መካከልም በኀይል ጎትቱት፡፡
آية رقم 48
ከዚያም «ከራሱ በላይ ከፈላ ውሃ ስቃይ አንቧቡበት፡፡»
آية رقم 49
ﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
«ቅመስ፤ አንተ አሸናፊው ክብሩ ነህና» (ይባላል)፡፡
آية رقم 50
ﮎﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
«ይህ ያ በእርሱ ትጠራጠሩበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 51
ﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ጥንቁቆቹ በእርግጥ በጸጥተኛ መኖሪያ ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 52
ﮛﮜﮝ
ﮞ
በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 53
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
ፊት ለፊት የተቅጣጩ ኾነው ከስስ ሐርና ከወፍራም ሐር ይለብሳሉ፡፡
آية رقم 54
ﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፤ ዓይናማዎች የኾኑን ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
آية رقم 55
ﮪﮫﮬﮭﮮ
ﮯ
በእርሷም ውስጥ የተማመኑ ኾነው፤ ከፍራፍሬ ሁሉ ያዝዛሉ፡፡
آية رقم 56
የፊተኛይቱን ሞት እንጅ (ዳግመኛ) በእርሷ ውስጥ ሞትን አይቀምሱም፡፡ የገሀነምንም ቅጣት (አላህ) ጠበቃቸው፡፡
آية رقم 57
ከጌታህ በኾነ ችሮታ (ጠበቃቸው)፡፡ ይህ እርሱ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
آية رقم 58
ﯦﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
(ቁርኣኑን) በቋንቋህም ያገራነው (ሕዝቦችህ) ይገነዘቡ ዘንድ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 59
ﯬﯭﯮ
ﯯ
ተጠባበቅም እነርሱ ተጠባባቂዎች ናቸውና፡፡
تقدم القراءة