ترجمة سورة العلق

الترجمة الأمهرية
ترجمة معاني سورة العلق باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
ሸንጎውንም ይጥራ፡፡
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡
Icon