ترجمة سورة العاديات

الترجمة الأمهرية
ترجمة معاني سورة العاديات باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
Icon