ترجمة معاني سورة الطور باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
ﰡ
آية رقم 1
ﮞ
ﮟ
በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡
آية رقم 2
ﮠﮡ
ﮢ
በተጻፈው መጽሐፍም፡፡
آية رقم 3
ﮣﮤﮥ
ﮦ
በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡
آية رقم 4
ﮧﮨ
ﮩ
በደመቀው ቤትም፡፡
آية رقم 5
ﮪﮫ
ﮬ
ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡
آية رقم 6
ﮭﮮ
ﮯ
በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡
آية رقم 7
ﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
آية رقم 8
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡
آية رقم 9
ﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡
آية رقم 10
ﯠﯡﯢ
ﯣ
ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡
آية رقم 11
ﯤﯥﯦ
ﯧ
ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡
آية رقم 12
ﯨﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡
آية رقم 13
ﯮﯯﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡
آية رقم 14
ﯵﯶﯷﯸﯹﯺ
ﯻ
ይህቺ ያቺ በእርሷ ታስተባብሉባት የነበራችሁት እሳት ናት፡፡
آية رقم 15
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ይህ (ፊት ትሉ እንደነበራችሁት) ድግምት ነውን? ወይስ እናንተ አታዩምን?
آية رقم 16
ግቧት ታገሱም ወይም አትታገሡ በእናንተ ላይ እኩል ነው፡፡ የምትምመነዱት ትሠሩት የነበራችሁትን (ፍዳ) ብቻ ነው (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 17
ﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
አላህን ፈሪዎቹ በእርግጥ በገነቶችና በጸጋ ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 18
ጌታቸው በሰጣቸው ጸጋ ተደሳቾች ኾነው (በገነት ውስጥ ናቸው)፡፡ የገሀነምንም ስቃይ ጌታቸው ጠበቃቸው፡፡
آية رقم 19
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
«ትሠሩት በነበራችሁት ምክንያት ተደሳቾች ኾናችሁ ብሉ፤ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 20
በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡
آية رقم 21
እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡
آية رقم 22
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ከሚሹትም ሁሉ እሸትንና ስጋን እንጨምርላቸዋለን፡፡
آية رقم 23
በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፡፡ በውስጧ ውድቅ ንግግርና መውወንጀልም የለም፡፡
آية رقم 24
ለነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ (ለማሳለፍ) ይዘዋወራሉ፡፡
آية رقم 25
ﯓﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
የሚጠያየቁ ኾነውም ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይዞራል፡፡
آية رقم 26
«እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን» ይላሉ፡፡
آية رقم 27
ﯡﯢﯣﯤﯥﯦ
ﯧ
«አላህም በእኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡
آية رقم 28
«እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበርን፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና» (ይላሉ)፡፡
آية رقم 29
(ሰዎችን) አስታውስም፡፡ አንተም በጌታህ ጸጋ ምክንያት ጠንቋይም ዕብድም አይደለህም፡፡
آية رقم 30
ይልቁንም የሞትን አደጋ በእርሱ የምንጠባበቅበት የኾነ ባለ ቅኔ ነው ይላሉን?
آية رقم 31
ﰄﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
«ተጠባበቁ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከሚጠባበቁት ነኝ» በላቸው፡፡
آية رقم 32
አእምሮዎቻቸው በዚህ ያዟቸዋልን? አይደለም በእውነቱ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦች ናቸው፡፡
آية رقم 33
ወይም «ቀጠፈው ይላሉን?» አይደለም፤ በእውነቱ አያምኑም፡፡
آية رقم 34
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
እውነተኞችም ቢኾኑ መሰሉ የኾነን ንግግር ያምጡ፡፡
آية رقم 35
ወይስ ያለ አንዳች (ፈጣሪ) ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን?
آية رقم 36
ወይስ ሰማያትንና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡
آية رقم 37
ወይስ የጌታህ ግምጃ ቤቶች እነርሱ ዘንድ ናቸውን? ወይስ እነርሱ አሸናፊዎች ናቸውን?
آية رقم 38
ወይስ ለእነርሱ በእርሱ ላይ (ከሰማይ) የሚያዳምጡበት መሰላል አላቸውን? አድማጫቸውም (ሰማሁ ቢል) ግልጽን አስረጅ ያምጣ፡፡
آية رقم 39
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን?
آية رقم 40
ወይስ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳው የተከበዱ ናቸውን?
آية رقم 41
ﮝﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
ወይስ ሩቁ ምስጢር እነርሱ ዘንድ ነውን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
آية رقم 42
ወይስ ተንኮልን (ባንተ) ይሻሉን? እነዚያም የካዱት እነርሱ በተንኮል ተሸናፊዎች ናቸው፡፡
آية رقم 43
ወይስ ለእነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ አላቸውን? አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡
آية رقم 44
ከሰማይም ቁራጭን (በእነርሱ ላይ) ወዳቂ ኾኖ ቢያዩ ኖሮ «ይህ የተደራረበ ደመና ነው» ይሉ ነበር፡፡
آية رقم 45
ያንንም በእርሱ የሚግገደሉበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡
آية رقم 46
ተንኮላቸው ከእነርሱ ምንንም የማይጠቅማቸውንና እነርሱም የማይርረዱበትን ቀን (እስከ ሚገናኙ ተዋቸው)፡፡
آية رقم 47
ለእነዚያ ለበደሉትም ከዚህ ሌላ ቅርብ ቅጣት አልላቸው፡፡ ግን አብዛኛዎቻቸው አያውቁም፡፡
آية رقم 48
ለጌታህ ፍርድም ታገሥ፡፡ አንተ በጥበቃችን ውስጥ ነህና፡፡ ጌታህንም በምትነሳ ጊዜ ከማመስገን ጋር አወድሰው፡፡
آية رقم 49
ﰋﰌﰍﰎﰏ
ﰐ
ከሌሊቱም አወድሰው፡፡ በከዋክብት መዳበቂያ ጊዜም (ንጋት ላይ አወድሰው)፡፡
تقدم القراءة