ترجمة معاني سورة الشمس باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
آية رقم 2

በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
آية رقم 3

በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
آية رقم 4

በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
آية رقم 5

በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
آية رقم 6

በምድሪቱም በዘረጋትም፤
آية رقم 7

በነፍስም ባስተካከላትም፤
آية رقم 8

አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
آية رقم 9

(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
آية رقم 10

(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
آية رقم 11

ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
آية رقم 12

ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
آية رقم 13

ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
آية رقم 14

አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
آية رقم 15

ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
تقدم القراءة