ترجمة معاني سورة الفجر باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


በጎህ እምላለሁ፡፡
آية رقم 2

በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
آية رقم 3

በጥንዱም በነጠላውም፡፡
آية رقم 4

በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
آية رقم 5

በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
آية رقم 7

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
آية رقم 8

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
آية رقم 9

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
آية رقم 10

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
آية رقم 11

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
آية رقم 12

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
آية رقم 13

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
آية رقم 14

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
آية رقم 19

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
آية رقم 20

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
آية رقم 22

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
آية رقم 24

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
آية رقم 25

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
آية رقم 26

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
آية رقم 27

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
آية رقم 28

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
آية رقم 29

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
آية رقم 30

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
تقدم القراءة