ترجمة معاني سورة الفجر باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭤ
ﭥ
በጎህ እምላለሁ፡፡
آية رقم 2
ﭦﭧ
ﭨ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
آية رقم 3
ﭩﭪ
ﭫ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
آية رقم 4
ﭬﭭﭮ
ﭯ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
آية رقم 5
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
آية رقم 6
ﭷﭸﭹﭺﭻﭼ
ﭽ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
آية رقم 7
ﭾﭿﮀ
ﮁ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
آية رقم 8
ﮂﮃﮄﮅﮆﮇ
ﮈ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
آية رقم 9
ﮉﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
آية رقم 10
ﮏﮐﮑ
ﮒ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
آية رقم 11
ﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
آية رقم 12
ﮘﮙﮚ
ﮛ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
آية رقم 13
ﮜﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
آية رقم 14
ﮢﮣﮤ
ﮥ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
آية رقم 15
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
آية رقم 16
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
آية رقم 17
ﯞﯟﯠﯡﯢﯣ
ﯤ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
آية رقم 18
ﯥﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
آية رقم 19
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
آية رقم 20
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
آية رقم 21
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
آية رقم 22
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤
آية رقم 23
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
آية رقم 24
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
آية رقم 25
ﭡﭢﭣﭤﭥ
ﭦ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
آية رقم 26
ﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
آية رقم 27
ﭬﭭﭮ
ﭯ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
آية رقم 28
ﭰﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
آية رقم 29
ﭶﭷﭸ
ﭹ
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
آية رقم 30
ﭺﭻ
ﭼ
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡
تقدم القراءة