ترجمة معاني سورة الليل باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
آية رقم 2

በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
آية رقم 3

ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
آية رقم 4

ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
آية رقم 5

የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
آية رقم 6

በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
آية رقم 7

ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
آية رقم 8

የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
آية رقم 9

በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
آية رقم 10

ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
آية رقم 11

በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
آية رقم 12

ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
آية رقم 13

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
آية رقم 14

የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
آية رقم 15

ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
آية رقم 16

ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
آية رقم 17

አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
آية رقم 18

ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
آية رقم 19

ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
آية رقم 20

ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
آية رقم 21

ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡
تقدم القراءة