ترجمة معاني سورة الإنشقاق باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭣﭤﭥ
ﭦ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
آية رقم 2
ﭧﭨﭩ
ﭪ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
آية رقم 3
ﭫﭬﭭ
ﭮ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
آية رقم 4
ﭯﭰﭱﭲ
ﭳ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
آية رقم 5
ﭴﭵﭶ
ﭷ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
آية رقم 6
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
آية رقم 7
ﮁﮂﮃﮄﮅ
ﮆ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
آية رقم 8
ﮇﮈﮉﮊ
ﮋ
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
آية رقم 9
ﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
آية رقم 10
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
آية رقم 11
ﮘﮙﮚ
ﮛ
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
آية رقم 12
ﮜﮝ
ﮞ
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
آية رقم 13
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
آية رقم 14
ﮥﮦﮧﮨﮩ
ﮪ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
آية رقم 15
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
آية رقم 16
ﯔﯕﯖ
ﯗ
አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
آية رقم 17
ﯘﯙﯚ
ﯛ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
آية رقم 18
ﯜﯝﯞ
ﯟ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
آية رقم 19
ﯠﯡﯢﯣ
ﯤ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
آية رقم 20
ﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
آية رقم 21
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)
آية رقم 22
ﯲﯳﯴﯵ
ﯶ
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
آية رقم 23
ﯷﯸﯹﯺ
ﯻ
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
آية رقم 24
ﯼﯽﯾ
ﯿ
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
آية رقم 25
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡
تقدم القراءة