ترجمة سورة الشمس

الترجمة الأمهرية
ترجمة معاني سورة الشمس باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية .
من تأليف: محمد صادق ومحمد الثاني حبيب .

በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
በነፍስም ባስተካከላትም፤
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
Icon