ترجمة معاني سورة المرسلات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﮑﮒ
ﮓ
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
آية رقم 2
ﮔﮕ
ﮖ
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
آية رقم 3
ﮗﮘ
ﮙ
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
آية رقم 4
ﮚﮛ
ﮜ
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
آية رقم 5
ﮝﮞ
ﮟ
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
آية رقم 6
ﮠﮡﮢ
ﮣ
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
آية رقم 7
ﮤﮥﮦ
ﮧ
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
آية رقم 8
ﮨﮩﮪ
ﮫ
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
آية رقم 9
ﮬﮭﮮ
ﮯ
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
آية رقم 10
ﮰﮱﯓ
ﯔ
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
آية رقم 11
ﯕﯖﯗ
ﯘ
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
آية رقم 12
ﯙﯚﯛ
ﯜ
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
آية رقم 13
ﯝﯞ
ﯟ
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
آية رقم 14
ﯠﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
آية رقم 15
ﯦﯧﯨ
ﯩ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 16
ﯪﯫﯬ
ﯭ
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
آية رقم 17
ﯮﯯﯰ
ﯱ
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
آية رقم 18
ﯲﯳﯴ
ﯵ
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
آية رقم 19
ﯶﯷﯸ
ﯹ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 20
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
آية رقم 21
ﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
آية رقم 22
ﭜﭝﭞ
ﭟ
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
آية رقم 23
ﭠﭡﭢ
ﭣ
መጣኞች ነን!
آية رقم 24
ﭤﭥﭦ
ﭧ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 25
ﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
آية رقم 26
ﭭﭮ
ﭯ
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
آية رقم 27
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
آية رقم 28
ﭸﭹﭺ
ﭻ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 29
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
آية رقم 30
ﮃﮄﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 31
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
آية رقم 32
ﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
آية رقم 33
ﮖﮗﮘ
ﮙ
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
آية رقم 34
ﮚﮛﮜ
ﮝ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 35
ﮞﮟﮠﮡ
ﮢ
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
آية رقم 36
ﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
آية رقم 37
ﮨﮩﮪ
ﮫ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 38
ﮬﮭﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
آية رقم 39
ﯔﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
آية رقم 40
ﯚﯛﯜ
ﯝ
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 41
ﯞﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 42
ﯤﯥﯦ
ﯧ
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 43
ﯨﯩﯪﯫﯬﯭ
ﯮ
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 44
ﯯﯰﯱﯲ
ﯳ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
آية رقم 45
ﯴﯵﯶ
ﯷ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 46
ﯸﯹﯺﯻﯼ
ﯽ
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
آية رقم 47
ﯾﯿﰀ
ﰁ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 48
ﰂﰃﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
آية رقم 49
ﰉﰊﰋ
ﰌ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 50
ﰍﰎﰏﰐ
ﰑ
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
تقدم القراءة