ترجمة معاني سورة عبس باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭑﭒ
ﭓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
آية رقم 2
ﭔﭕﭖ
ﭗ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
آية رقم 3
ﭘﭙﭚﭛ
ﭜ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
آية رقم 4
ﭝﭞﭟﭠ
ﭡ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
آية رقم 5
ﭢﭣﭤ
ﭥ
የተብቃቃው ሰውማ፤
آية رقم 6
ﭦﭧﭨ
ﭩ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
آية رقم 7
ﭪﭫﭬﭭ
ﭮ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
آية رقم 8
ﭯﭰﭱﭲ
ﭳ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
آية رقم 9
ﭴﭵ
ﭶ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
آية رقم 10
ﭷﭸﭹ
ﭺ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
آية رقم 11
ﭻﭼﭽ
ﭾ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
آية رقم 12
ﭿﮀﮁ
ﮂ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
آية رقم 13
ﮃﮄﮅ
ﮆ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 14
ﮇﮈ
ﮉ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
آية رقم 15
ﮊﮋ
ﮌ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
آية رقم 16
ﮍﮎ
ﮏ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
آية رقم 17
ﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
آية رقم 18
ﮕﮖﮗﮘ
ﮙ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
آية رقم 19
ﮚﮛﮜﮝ
ﮞ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
آية رقم 20
ﮟﮠﮡ
ﮢ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
آية رقم 21
ﮣﮤﮥ
ﮦ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
آية رقم 22
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
آية رقم 23
ﮬﮭﮮﮯﮰ
ﮱ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
آية رقم 24
ﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
آية رقم 25
ﯘﯙﯚﯛ
ﯜ
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
آية رقم 26
ﯝﯞﯟﯠ
ﯡ
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
آية رقم 27
ﯢﯣﯤ
ﯥ
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
آية رقم 28
ﯦﯧ
ﯨ
ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
آية رقم 29
ﯩﯪ
ﯫ
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
آية رقم 30
ﯬﯭ
ﯮ
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
آية رقم 31
ﯯﯰ
ﯱ
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
آية رقم 32
ﯲﯳﯴ
ﯵ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
آية رقم 33
ﯶﯷﯸ
ﯹ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
آية رقم 34
ﯺﯻﯼﯽﯾ
ﯿ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
آية رقم 35
ﰀﰁ
ﰂ
ከናቱም ካባቱም፤
آية رقم 36
ﰃﰄ
ﰅ
ከሚስቱም ከልጁም፤
آية رقم 37
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋ
ﰌ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
آية رقم 38
ﰍﰎﰏ
ﰐ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
آية رقم 39
ﰑﰒ
ﰓ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
آية رقم 40
ﰔﰕﰖﰗ
ﰘ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
آية رقم 41
ﭑﭒ
ﭓ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
آية رقم 42
ﭔﭕﭖﭗ
ﭘ
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
تقدم القراءة