ترجمة معاني سورة عبس باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
آية رقم 3

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
آية رقم 4

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
آية رقم 6

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
آية رقم 7

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
آية رقم 9

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
آية رقم 10

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
آية رقم 11

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
آية رقم 12

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
آية رقم 13

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 14

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
آية رقم 15

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
آية رقم 16

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
آية رقم 17

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
آية رقم 18

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
آية رقم 19

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
آية رقم 20

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
آية رقم 21

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
آية رقم 22

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
آية رقم 23

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
آية رقم 25

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
آية رقم 26

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
آية رقم 27

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
آية رقم 28

ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤
آية رقم 29

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
آية رقم 30

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
آية رقم 31

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
آية رقم 32

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
آية رقم 33

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
آية رقم 35

ከናቱም ካባቱም፤
آية رقم 36

ከሚስቱም ከልጁም፤
آية رقم 37

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
آية رقم 38

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
آية رقم 39

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
آية رقم 40

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
آية رقم 41

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
آية رقم 42

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡
تقدم القراءة