ترجمة معاني سورة النازعات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﮢﮣ
ﮤ
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
آية رقم 2
ﮥﮦ
ﮧ
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
آية رقم 3
ﮨﮩ
ﮪ
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
آية رقم 4
ﮫﮬ
ﮭ
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
آية رقم 5
ﮮﮯ
ﮰ
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
آية رقم 6
ﮱﯓﯔ
ﯕ
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
آية رقم 7
ﯖﯗ
ﯘ
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
آية رقم 8
ﯙﯚﯛ
ﯜ
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 9
ﯝﯞ
ﯟ
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
آية رقم 10
ﯠﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
آية رقم 11
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
آية رقم 12
ﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
آية رقم 13
ﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
آية رقم 14
ﯶﯷﯸ
ﯹ
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
آية رقم 15
ﯺﯻﯼﯽ
ﯾ
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
آية رقم 16
ﯿﰀﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
آية رقم 17
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
آية رقم 18
ﭗﭘﭙﭚﭛﭜ
ﭝ
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
آية رقم 19
ﭞﭟﭠﭡ
ﭢ
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
آية رقم 20
ﭣﭤﭥ
ﭦ
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
آية رقم 21
ﭧﭨ
ﭩ
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
آية رقم 22
ﭪﭫﭬ
ﭭ
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
آية رقم 23
ﭮﭯ
ﭰ
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
آية رقم 24
ﭱﭲﭳﭴ
ﭵ
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
آية رقم 25
ﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
آية رقم 26
ﭼﭽﭾﭿﮀﮁ
ﮂ
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
آية رقم 27
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
آية رقم 28
ﮋﮌﮍ
ﮎ
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
آية رقم 29
ﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
آية رقم 30
ﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
آية رقم 31
ﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
آية رقم 32
ﮞﮟ
ﮠ
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
آية رقم 33
ﮡﮢﮣ
ﮤ
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
آية رقم 34
ﮥﮦﮧﮨ
ﮩ
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
آية رقم 35
ﮪﮫﮬﮭﮮ
ﮯ
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
آية رقم 36
ﮰﮱﯓﯔ
ﯕ
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
آية رقم 37
ﯖﯗﯘ
ﯙ
የካደ ሰውማ፣
آية رقم 38
ﯚﯛﯜ
ﯝ
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
آية رقم 39
ﯞﯟﯠﯡ
ﯢ
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
آية رقم 40
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
آية رقم 41
ﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
آية رقم 42
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
آية رقم 43
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
آية رقم 44
ﯽﯾﯿ
ﰀ
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 45
ﰁﰂﰃﰄﰅ
ﰆ
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
آية رقم 46
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
تقدم القراءة