ترجمة معاني سورة النازعات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
آية رقم 2

በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
آية رقم 3

መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
آية رقم 4

መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
آية رقم 5

ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
آية رقم 6

ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
آية رقم 7

ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
آية رقم 8

በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 9

ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
آية رقم 10

«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
آية رقم 11

«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
آية رقم 12

«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
آية رقم 13

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
آية رقم 14

ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
آية رقم 17

ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
آية رقم 18

በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
آية رقم 19

«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
آية رقم 20

ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
آية رقم 21

አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
آية رقم 22

ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
آية رقم 23

(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
آية رقم 24

አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
آية رقم 25

አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
آية رقم 26

በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
آية رقم 27

ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
آية رقم 28

ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
آية رقم 29

ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
آية رقم 30

ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
آية رقم 31

ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
آية رقم 32

ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
آية رقم 33

ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
آية رقم 35

ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
آية رقم 36

ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
آية رقم 38

ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
آية رقم 39

ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
آية رقم 41

ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
آية رقم 42

«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
آية رقم 43

አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
آية رقم 44

(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 45

አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
تقدم القراءة