ترجمة معاني سورة نوح باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
እኛ ኑሕን «ሕዝቦችህን አሳማሚ ቅጣት ሳይመጣባቸው በፊት አስጠንቅቅ በማለት ወደ ሕዝቦቹ ላክነው፡፡»
آية رقم 2
ﮇﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
(እርሱም) አለ «ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ለእናንተ ገላጭ የኾንኩ አስጠንቃቂ ነኝ፡፡
آية رقم 3
ﮎﮏﮐﮑﮒ
ﮓ
«አላህን ተገዙት፣ ፍሩትም፣ ታዘዙኝም በማለት፤ (አስጠንቃቂ ነኝ)፡፡
آية رقم 4
«ለእናንተ ከኀጢኣቶቻችሁ ይምራልና፡፡ ወደተወሰነው ጊዜም ያቆያችኋል፡፡ የአላህ (የወሰነው) ጊዜ በመጣ ወቅት አይቆይም፡፡ የምታውቁት ብትኾኑ ኖሮ (በታዘዛችሁ ነበር)፡፡»
آية رقم 5
(ስለ ተቃወሙትም) «አለ ጌታዬ ሆይ! እኔ ሌሊትም ቀንም ሕዝቦቼን ጠራሁ፡፡
آية رقم 6
ﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
«ጥሪየም መሸሽን እንጅ ሌላ አልጨመረላቸውም፡፡
آية رقم 7
«እኔም ለእነርሱ ትምር ዘንድ (ወደ እምነት) በጠራኋቸው ቁጥር ጣቶቻቸውን በጆሮዎቻቸው ውስጥ አደረጉ፡፡ ልብሶቻቸውንም ተከናነቡ፡፡ (በመጥፎ ሥራቸው ላይ) ዘወተሩም፡፡ (ያለ ልክ) መኩራትንም ኮሩ፡፡
آية رقم 8
ﯧﯨﯩﯪ
ﯫ
«ከዚያም እኔ በጩኸት ጠራኋቸው፡፡
آية رقم 9
«ከዚያም እኔ ለእነርሱ ገለጽኩ፡፡ ለእነርሱም መመስጠርን መሰጠርኩ
آية رقم 10
ﯴﯵﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
«አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡
آية رقم 11
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
«በእናንተ ላይ ዝናምን ተከታታይ አድርጎ ይልካል፡፡
آية رقم 12
«በገንዘቦችና በልጆችም ይለግሰላችኋል፡፡ ለእናንተም አትክልቶችን ያደርግላችኋል፡፡ ለእናንተም ወንዞችን ያደርግላችኋል፡፡»
آية رقم 13
ﭠﭡﭢﭣﭤﭥ
ﭦ
ለአላህ ልቅናን የማትሹት ለእናንተ ምን አላችሁ?
آية رقم 14
ﭧﭨﭩ
ﭪ
በልዩ ልዩ ኹኔታዎች በእርግጥ የፈጠራችሁ ሲኾን፡፡
آية رقم 15
አላህ ሰባትን ሰማያት አንዱ ካንዱ በላይ ሲኾን እንዴት እንደፈጠረ አታዩምን?
آية رقم 16
በውስጣቸውም ጨረቃን አብሪ አደረገ፡፡ ፀሐይንም ብርሃን አደረገ፡፡
آية رقم 17
ﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
አላህም ከምድር ማብቀልን አበቀላችሁ፡፡
آية رقم 18
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
ከዚያም በውስጧ ይመልሳችኋል፡፡ ማውጣትንም ያወጣችኋል፡፡
آية رقم 19
ﮈﮉﮊﮋﮌ
ﮍ
አላህም ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ አደረጋት፡፡
آية رقم 20
ﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ከእርሷ ሰፋፊዎችን መንገዶች ትገቡ ዘንድ፡፡
آية رقم 21
ኑሕ አለ፡- «ጌታዬ ሆይ! እነሱ አምመጹብኝ፡፡ ገንዘቡና ልጁም ከጥፋት በስተቀር ያልጨመረለትን ሰው ተከተሉ፡፡
آية رقم 22
ﮡﮢﮣ
ﮤ
«ታላቅንም ተንኮል የመከሩትን ሰዎች» (ተከተሉ)፡፡
آية رقم 23
አሉም «አምላኮቻችሁን አትተዉ፡፡ ወድንም፣ ሱዋዕንም፣ የጉሥንም፣ የዑቅንም ነስርንም አትተው፡፡
آية رقم 24
«በእርግጥም ብዙዎችን አሳሳቱ፡፡ ከሓዲዎችንም ጥመትን እንጅ ሌላን አትጨምርላቸው» (አለ)፡፡
آية رقم 25
በኀጢኣቶቻቸው ምክንያት ተሰጠሙ፡፡ እሳትንም እንዲገቡ ተደረጉ፡፡ ለእነርሱም ከአላህ ሌላ የኾኑ ረዳቶችን አላገኙም፡፡
آية رقم 26
ኑሕም አለ «ጌታዬ ሆይ! ከከሓዲዎቹ በምድር ላይ አንድንም አትተው፡፡
آية رقم 27
«አንተ ብትተዋቸው ባሮችህን ያሳስታሉና፡፡ ኀጢኣተኛ ከሓዲንም እንጅ ሌላን አይወልዱም፡፡
آية رقم 28
«ጌታዬ ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ምእመን ኾኖ በቤቴ ለገባም ሰው ሁሉ ለምእመናንና ለምእምናትም ምሕረት አድርግ፡፡ ከሓዲዎችንም ከጥፋት በቀር አትጨምርላቸው፤» (አለ)፡፡
تقدم القراءة