ترجمة معاني سورة الإنفطار باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
آية رقم 2

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
آية رقم 3

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
آية رقم 4

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
آية رقم 5

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
آية رقم 7

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
آية رقم 8

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
آية رقم 9

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
آية رقم 10

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
آية رقم 11

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
آية رقم 12

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
آية رقم 13

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 14

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 15

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
آية رقم 16

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
آية رقم 17

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
آية رقم 18

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
تقدم القراءة