ترجمة سورة الإنفطار

Sadiq and Sani - Amharic translation
ترجمة معاني سورة الإنفطار باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation .


ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
Icon