ترجمة معاني سورة الصافات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
آية رقم 2

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
آية رقم 3

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
آية رقم 4

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
آية رقم 5

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
آية رقم 6

እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
آية رقم 7

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
آية رقم 9

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
آية رقم 10

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
آية رقم 12

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
آية رقم 13

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
آية رقم 14

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
آية رقم 15

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 16

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
آية رقم 17

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
آية رقم 18

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
آية رقم 19

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
آية رقم 20

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
آية رقم 21

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 22

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
آية رقم 23

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
آية رقم 24

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
آية رقم 25

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 26

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
آية رقم 27

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
آية رقم 28

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
آية رقم 29

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
آية رقم 31

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
آية رقم 32

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
آية رقم 33

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 34

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
آية رقم 36

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
آية رقم 37

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
آية رقم 38

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
آية رقم 39

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
آية رقم 40

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
آية رقم 41

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
آية رقم 42

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
آية رقم 43

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
آية رقم 44

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
آية رقم 45

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
آية رقم 46

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
آية رقم 47

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
آية رقم 48

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
آية رقم 49

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
آية رقم 50

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
آية رقم 51

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
آية رقم 52

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
آية رقم 53

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
آية رقم 54

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
آية رقم 55

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
آية رقم 56

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
آية رقم 57

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
آية رقم 58

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
آية رقم 59

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
آية رقم 60

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
آية رقم 62

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
آية رقم 63

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
آية رقم 64

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
آية رقم 65

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
آية رقم 66

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
آية رقم 67

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
آية رقم 68

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
آية رقم 69

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
آية رقم 70

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
آية رقم 71

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
آية رقم 72

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
آية رقم 73

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
آية رقم 74

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 75

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
آية رقم 76

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
آية رقم 77

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
آية رقم 78

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
آية رقم 79

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
آية رقم 80

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
آية رقم 81

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
آية رقم 82

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
آية رقم 83

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
آية رقم 84

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
آية رقم 85

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
آية رقم 86

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
آية رقم 87

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
آية رقم 88

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
آية رقم 89

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
آية رقم 90

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
آية رقم 91

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
آية رقم 92

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
آية رقم 93

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
آية رقم 94

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
آية رقم 95

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
آية رقم 96

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
آية رقم 97

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
آية رقم 98

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
آية رقم 99

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
آية رقم 100

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
آية رقم 101

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
آية رقم 103

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
آية رقم 104

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
آية رقم 105

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
آية رقم 106

ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
آية رقم 107

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
آية رقم 108

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
آية رقم 109

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
آية رقم 110

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
آية رقم 111

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
آية رقم 112

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
آية رقم 114

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
آية رقم 115

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
آية رقم 116

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
آية رقم 117

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
آية رقم 118

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
آية رقم 119

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
آية رقم 120

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
آية رقم 121

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
آية رقم 122

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
آية رقم 123

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
آية رقم 124

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
آية رقم 125

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
آية رقم 126

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
آية رقم 127

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
آية رقم 128

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 129

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
آية رقم 130

ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
آية رقم 131

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
آية رقم 132

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
آية رقم 133

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
آية رقم 134

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
آية رقم 135

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
آية رقم 136

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
آية رقم 137

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
آية رقم 138

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
آية رقم 139

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
آية رقم 140

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
آية رقم 141

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
آية رقم 142

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
آية رقم 143

እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
آية رقم 144

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
آية رقم 145

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
آية رقم 146

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
آية رقم 147

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡
آية رقم 148

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
آية رقم 149

(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
آية رقم 150

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
آية رقم 151

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
آية رقم 152

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
آية رقم 153

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
آية رقم 154

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
آية رقم 155

አትገነዘቡምን?
آية رقم 156

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
آية رقم 157

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
آية رقم 160

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
آية رقم 161

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
آية رقم 162

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
آية رقم 163

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
آية رقم 164

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
آية رقم 165

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
آية رقم 166

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
آية رقم 167

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
آية رقم 168

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
آية رقم 169

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
آية رقم 170

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
آية رقم 171

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
آية رقم 172

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
آية رقم 173

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
آية رقم 174

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
آية رقم 175

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
آية رقم 176

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
آية رقم 177

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
آية رقم 178

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
آية رقم 179

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
آية رقم 180

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
آية رقم 181

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
آية رقم 182

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
تقدم القراءة