ترجمة معاني سورة القيامة باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
آية رقم 2

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
آية رقم 3

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
آية رقم 4

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
آية رقم 5

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
آية رقم 6

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
آية رقم 8

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
آية رقم 9

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
آية رقم 10

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
آية رقم 11

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
آية رقم 12

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 13

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
آية رقم 14

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
آية رقم 15

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
آية رقم 16

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
آية رقم 17

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
آية رقم 18

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
آية رقم 19

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
آية رقم 20

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
آية رقم 21

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
آية رقم 22

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 23

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
آية رقم 24

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
آية رقم 25

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
آية رقم 26

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
آية رقم 27

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
آية رقم 28

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
آية رقم 29

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
آية رقم 30

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
آية رقم 32

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
آية رقم 33

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
آية رقم 34

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
آية رقم 35

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
آية رقم 37

የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
آية رقم 38

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
آية رقم 39

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
آية رقم 40

ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
تقدم القراءة