ترجمة معاني سورة البروج باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
آية رقم 2

በተቀጠረው ቀንም፤
آية رقم 3

በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
آية رقم 4

የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
آية رقم 5

የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
آية رقم 6

እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
آية رقم 7

እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡

ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡

በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡

እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
آية رقم 12

የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
آية رقم 13

እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
آية رقم 14

እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
آية رقم 15

የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
آية رقم 16

የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
آية رقم 18

የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
آية رقم 19

በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 20

አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
آية رقم 21

ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
آية رقم 22

የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
تقدم القراءة