ترجمة معاني سورة البروج باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭛﭜﭝ
ﭞ
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
آية رقم 2
ﭟﭠ
ﭡ
በተቀጠረው ቀንም፤
آية رقم 3
ﭢﭣ
ﭤ
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
آية رقم 4
ﭥﭦﭧ
ﭨ
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
آية رقم 5
ﭩﭪﭫ
ﭬ
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
آية رقم 6
ﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
آية رقم 7
ﭲﭳﭴﭵﭶﭷ
ﭸ
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
آية رقم 8
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
آية رقم 9
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
آية رقم 10
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
آية رقم 11
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
آية رقم 12
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
آية رقم 13
ﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
آية رقم 14
ﯙﯚﯛ
ﯜ
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
آية رقم 15
ﯝﯞﯟ
ﯠ
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
آية رقم 16
ﯡﯢﯣ
ﯤ
የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
آية رقم 17
ﯥﯦﯧﯨ
ﯩ
የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
آية رقم 18
ﯪﯫ
ﯬ
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
آية رقم 19
ﯭﯮﯯﯰﯱ
ﯲ
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 20
ﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
آية رقم 21
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
آية رقم 22
ﯽﯾﯿ
ﰀ
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
تقدم القراءة