ترجمة معاني سورة المعارج باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
آية رقم 2

በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
آية رقم 3

የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡

መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
آية رقم 5

መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
آية رقم 6

እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
آية رقم 7

እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
آية رقم 8

ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
آية رقم 9

ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
آية رقم 10

ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡

(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
آية رقم 12

በሚስቱም በወንድሙም፡፡
آية رقم 13

በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
آية رقم 14

በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
آية رقم 15

ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
آية رقم 16

የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
آية رقم 17

(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
آية رقم 18

ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
آية رقم 20

ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
آية رقم 21

መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
آية رقم 22

ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 23

እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 24

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
آية رقم 25

ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
آية رقم 26

እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
آية رقم 27

እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 28

የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
آية رقم 29

እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡

በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
آية رقم 31

ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
آية رقم 32

እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 33

እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
آية رقم 34

እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
آية رقم 35

እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
آية رقم 36

ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
آية رقم 37

ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
آية رقم 38

ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
آية رقم 39

ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
آية رقم 40

በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
آية رقم 41

ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
آية رقم 42

ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡

ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡

ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
تقدم القراءة