ترجمة معاني سورة المعارج باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
آية رقم 2
ﯔﯕﯖﯗ
ﯘ
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
آية رقم 3
ﯙﯚﯛﯜ
ﯝ
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
آية رقم 4
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
آية رقم 5
ﯪﯫﯬ
ﯭ
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
آية رقم 6
ﯮﯯﯰ
ﯱ
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
آية رقم 7
ﯲﯳ
ﯴ
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
آية رقم 8
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
آية رقم 9
ﯺﯻﯼ
ﯽ
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
آية رقم 10
ﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
آية رقم 11
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
آية رقم 12
ﭜﭝ
ﭞ
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
آية رقم 13
ﭟﭠﭡ
ﭢ
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
آية رقم 14
ﭣﭤﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
آية رقم 15
ﭪﭫﭬﭭ
ﭮ
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
آية رقم 16
ﭯﭰ
ﭱ
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
آية رقم 17
ﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
آية رقم 18
ﭷﭸ
ﭹ
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
آية رقم 19
ﭺﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
آية رقم 20
ﮀﮁﮂﮃ
ﮄ
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
آية رقم 21
ﮅﮆﮇﮈ
ﮉ
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
آية رقم 22
ﮊﮋ
ﮌ
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 23
ﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 24
ﮓﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
آية رقم 25
ﮙﮚ
ﮛ
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
آية رقم 26
ﮜﮝﮞﮟ
ﮠ
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
آية رقم 27
ﮡﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 28
ﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
آية رقم 29
ﮮﮯﮰﮱ
ﯓ
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 30
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
آية رقم 31
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
آية رقم 32
ﯧﯨﯩﯪﯫ
ﯬ
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 33
ﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
آية رقم 34
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
آية رقم 35
ﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
آية رقم 36
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
آية رقم 37
ﰃﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
آية رقم 38
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
آية رقم 39
ﰒﰓﰔﰕﰖﰗ
ﰘ
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
آية رقم 40
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
آية رقم 41
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
آية رقم 42
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
آية رقم 43
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
آية رقم 44
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
تقدم القراءة