ترجمة معاني سورة المعارج
 باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
            .
            
                                    من تأليف: 
                                            محمد صادق ومحمد الثاني حبيب
                                                            .
                                                
            
                                                                                                            ﰡ
                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    (ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    (ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
                                                                         
                                                                                                                                        
                    
                                                                                    ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡