ترجمة معاني سورة الحاقة باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
آية رقم 2

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
آية رقم 3

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
آية رقم 4

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
آية رقم 5

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
آية رقم 6

ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
آية رقم 9

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
آية رقم 10

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
آية رقم 11

እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
آية رقم 12

ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
آية رقم 14

ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
آية رقم 15

በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
آية رقم 16

ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡

መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
آية رقم 18

በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
آية رقم 20

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
آية رقم 21

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
آية رقم 22

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
آية رقم 23

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
آية رقم 24

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡

መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
آية رقم 26

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
آية رقم 27

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
آية رقم 28

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
آية رقم 29

«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
آية رقم 30

«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
آية رقم 31

«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
آية رقم 32

«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
آية رقم 33

እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
آية رقم 34

ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
آية رقم 36

ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
آية رقم 37

ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
آية رقم 38

በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
آية رقم 40

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
آية رقم 41

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
آية رقم 42

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
آية رقم 43

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
آية رقم 44

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
آية رقم 45

በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
آية رقم 46

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
آية رقم 47

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
آية رقم 48

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
آية رقم 49

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
آية رقم 50

እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
آية رقم 51

እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
آية رقم 52

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
تقدم القراءة