ترجمة معاني سورة الحاقة باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﮯ
ﮰ
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
آية رقم 2
ﮱﯓ
ﯔ
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
آية رقم 3
ﯕﯖﯗﯘ
ﯙ
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
آية رقم 4
ﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
آية رقم 5
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
آية رقم 6
ﯤﯥﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
آية رقم 7
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
آية رقم 8
ﯼﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
آية رقم 9
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
آية رقم 10
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
آية رقم 11
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
آية رقم 12
ﭧﭨﭩﭪﭫﭬ
ﭭ
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
آية رقم 13
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
آية رقم 14
ﭵﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
آية رقم 15
ﭼﭽﭾ
ﭿ
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
آية رقم 16
ﮀﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
آية رقم 17
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
آية رقم 18
ﮑﮒﮓﮔﮕﮖ
ﮗ
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
آية رقم 19
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
آية رقم 20
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
آية رقم 21
ﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
آية رقم 22
ﮭﮮﮯ
ﮰ
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
آية رقم 23
ﮱﯓ
ﯔ
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
آية رقم 24
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 25
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
آية رقم 26
ﯩﯪﯫﯬ
ﯭ
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
آية رقم 27
ﯮﯯﯰ
ﯱ
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
آية رقم 28
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
آية رقم 29
ﯸﯹﯺ
ﯻ
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
آية رقم 30
ﯼﯽ
ﯾ
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
آية رقم 31
ﯿﰀﰁ
ﰂ
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
آية رقم 32
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
آية رقم 33
ﰋﰌﰍﰎﰏﰐ
ﰑ
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
آية رقم 34
ﰒﰓﰔﰕﰖ
ﰗ
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
آية رقم 35
ﰘﰙﰚﰛﰜ
ﰝ
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
آية رقم 36
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
آية رقم 37
ﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
آية رقم 38
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
آية رقم 39
ﭡﭢﭣ
ﭤ
በማታዩትም ነገር፡፡
آية رقم 40
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
آية رقم 41
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
آية رقم 42
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
آية رقم 43
ﭻﭼﭽﭾ
ﭿ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
آية رقم 44
ﮀﮁﮂﮃﮄ
ﮅ
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
آية رقم 45
ﮆﮇﮈ
ﮉ
በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
آية رقم 46
ﮊﮋﮌﮍ
ﮎ
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
آية رقم 47
ﮏﮐﮑﮒﮓﮔ
ﮕ
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
آية رقم 48
ﮖﮗﮘ
ﮙ
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
آية رقم 49
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
آية رقم 50
ﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
آية رقم 51
ﮥﮦﮧ
ﮨ
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
آية رقم 52
ﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
تقدم القراءة