ترجمة معاني سورة الذاريات باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﯤﯥ
ﯦ
መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡
آية رقم 2
ﯧﯨ
ﯩ
ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡
آية رقم 3
ﯪﯫ
ﯬ
ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡
آية رقم 4
ﯭﯮ
ﯯ
ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡
آية رقم 5
ﯰﯱﯲ
ﯳ
የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡
آية رقم 6
ﯴﯵﯶ
ﯷ
(እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡
آية رقم 7
ﭑﭒﭓ
ﭔ
የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
آية رقم 8
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡
آية رقم 9
ﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡
آية رقم 10
ﭟﭠ
ﭡ
በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡
آية رقم 11
ﭢﭣﭤﭥﭦ
ﭧ
እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡
آية رقم 12
ﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡
آية رقم 13
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
(እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡
آية رقم 14
«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነው» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 15
ﭻﭼﭽﭾﭿ
ﮀ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 16
ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡
آية رقم 17
ﮌﮍﮎﮏﮐﮑ
ﮒ
ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡
آية رقم 18
ﮓﮔﮕ
ﮖ
በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡
آية رقم 19
ﮗﮘﮙﮚﮛ
ﮜ
በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡
آية رقم 20
ﮝﮞﮟﮠ
ﮡ
በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡
آية رقم 21
ﮢﮣﮤﮥﮦ
ﮧ
በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?›
آية رقم 22
ﮨﮩﮪﮫﮬ
ﮭ
ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 23
በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡
آية رقم 24
ﯙﯚﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን?
آية رقم 25
በእርሱ ላይ በገቡና «ሰለም» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ «ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤» አላቸው፡፡
آية رقم 26
ﯫﯬﯭﯮﯯﯰ
ﯱ
ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡
آية رقم 27
ﯲﯳﯴﯵﯶ
ﯷ
ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ «አትበሉም ወይ?» አላቸው፡፡
آية رقم 28
ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡
آية رقم 29
ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም፡፡
آية رقم 30
እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ «እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡
آية رقم 31
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?» አላቸው፡፡
آية رقم 32
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
(እነርሱም) አሉ፡- «እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡»
آية رقم 33
ﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡
آية رقم 34
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡
آية رقم 35
ﭪﭫﭬﭭﭮﭯ
ﭰ
ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡
آية رقم 36
በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡
آية رقم 37
በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡
آية رقم 38
በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡
آية رقم 39
ﮊﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» አለም፡፡
آية رقم 40
እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡
آية رقم 41
በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
آية رقم 42
በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡
آية رقم 43
በሰሙድም ለእነርሱ «እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡
آية رقم 44
ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡
آية رقم 45
መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡
آية رقم 46
የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡
آية رقم 47
ﯰﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
آية رقم 48
ﯶﯷﯸﯹ
ﯺ
ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)
آية رقم 49
ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡
آية رقم 50
«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡
آية رقم 51
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡
آية رقم 52
(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡
آية رقم 53
በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡
آية رقم 54
ﭧﭨﭩﭪﭫ
ﭬ
ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡
آية رقم 55
ﭭﭮﭯﭰﭱ
ﭲ
ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡
آية رقم 56
ﭳﭴﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
آية رقم 57
ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡
آية رقم 58
አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡
آية رقم 59
ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡
آية رقم 60
ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡
تقدم القراءة